ልጥፎች

ኢትዮጵያ ሥመ - ጥር፤ ጀግና ጨዋ የሠራዊት መሪ ነበራት።

ምስል
  ኢትዮጵያ ሥመ - ጥር፤ ጀግና ጨዋ የሠራዊት መሪ ነበራት።    "አቤቱ ንጹህ ልብን ፍጠርልኝ።" አሜን።    በዘመኔ ያየኋቸው ቆፍጣና፤ ንቁ፤ ትጉህ፤ ዲስፕሊንድ የኢትዮጵያ የሠራዊት መሪወች፤ የሠራዊቱ አባሎች አቋቋማቸው፤ አረማመዳቸው፤ የአነጋገር ዘይቤያቸው #ቁጥብነት ፤ ሥርዓታቸው፤ የአለባበሳቸው ጥራት ፈጽሞ አይረሳኝም።    በእኔ የልጅነት - ዘመን፤ በእኔ የወጣትነት - ዘመን፤ በእኔ የሥራ - ዘመን፤ በእኔ የኃላፊነት እና የተጠያቂነት - ዘመን ያዬኋቸው #ቆፍጣና ፤ #ጥንቁቅ ፤ ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያዊነትን ብቻ #መለዮቸው ያደረጉ ድንቆች አይረሱኝም። ኢትዮጵያ ብቃት ያለው ሠራዊት ነበራት። ያው የኢትዮጵያ የችግር ምንጭ የፖለቲካ ኢሊቱ የአመራር ጥበብ ማነስ ይሁን ሌላ ብቻ በጣም ብዙ መስዋዕትነትን የከፈሉ ዕንቁ የጦር መኮንኖች፤ የሠራዊቱ አባላቱም ህወሃት ሥልጣን ሲይዝ በተናቸው። ያ በተመክሮ፤ በዕውቀት፤ በብቃት የሠለጠነ ተቋም በአመዛኙ በህወሃት አማተር ሠራዊት ተተካ። በጫካ ዲስፕሊን ነገሩ ሁሉ ተቀመመ።    የኢትዮጵያ ሊቃናት ስለምን #አድካሚውን መንገድ እንደሚመርጡ ባይገባኝም፤ የትውልዱ ድካም እና ልፋት ባክኖ መቅረቱ ግን በእጅጉ ያንገበግበኛል። በየቤታችን ወንድሞቻችን ገብረናል በናቅፋ በአፋቤት በርሃ።   የሆነ ሆኖ ትልቅ ሰው #አይሞትም ህያው ነው። ክቡርነታቸው ልጆችም ስላላቸውም ተመስገን ነው። እኒህን ታላቅ ሰው ኢትዮጵያ ስታጣ ኢትዮጵያን እግዚአብሄር #ያጽናሽ ማለት ይገባል።   በተጨማሪም ለቤተሰብ፤ ለወዳጅ ዘመድንም መጽናናቱን እመኛለሁኝ። ከእኛ የቀደመው ትውልድ መራራ ስንብት እያደረገ ነው። አይዋ አይለዬ #ሞት ወደ እኛም እየገሰገሰ ነው። ...

A+ #ብራቦ አማራ ክልል። በዘመንህ እንዲህ የልብ አድርስ ተግባር ብየ እምመሰክርልህ አልነበረኽም።

ምስል
  A+ #ብራቦ አማራ ክልል። በዘመንህ እንዲህ የልብ አድርስ ተግባር ብየ እምመሰክርልህ አልነበረኽም።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።   ምዕራፍ ፲፯     #የማንነት #ቀውስ እና ሙሁርነት #ግብግብ ገጠሙ። "ግዕዝ የሞተ ቋንቋ ነው ዶር በድሉ ዋቅጅራ።" መሃከነ!   አይዋ እከሌ፤ ቢማሩ --- ቢመራመሩ ግዕዝ በአበጃት አገር ላይ ነው። ፈላስፋ ቢሆኑ ሳይንቲስት፤ ኤክስፐርት ቢሆኑ የዩንቨርስቲ መምህር፤ ከመጨረሻው የዕውቀት፤ የሥልጣን መንበር ላይም ቢደረሰም፤ የዘመን ጋሻነትም ቢኖር፤ በመልክ፤ በቁመና የሚያስጎመጁ ዓይነት ሸበላም ቢሆኑም #የማንነት #ቀውስ ካለ የሃሳብህ ክሳትን ቀጫጫነትን እርስወን መዝኖ መዝኖ አደባባይ ላይ #ያሰጣል ።    #ሙጃ ሃሳብ ለትውልድ #የአረም ክርም ነው። የግዕዝ ቋንቋ ቋንቋ ብቻ አይደለም #የሚስጢር ፤ #የፈውስ ፤ #የስኬት #ማህጸን እንጂ። ለእርስወ ይቀራል እንጂ እጬጌው ግዕዝ በግሎባል ደረጃ ከፍ ብሎ ከተቀመጠበት መንበር ንቅንቅ ሊያደርጉት ከቶውንም አይቻልም። #ቁጭላ ሃሳብ ቋት አይገፋምና። በትንታ አጋዢነት በኖ ይቀራል።    ልባሞቹ አገራት፤ ትንግርቶቹ - አህጉራት፤ ሥልጣኔያቸው የተቀመመው በግዕዝ የሚስጥራት ጥልቅ #ልቀት ነው። ለዚህም ነው ቋንቋውን ልጆቻቸው ይማሩት ዘንድ በከፍተኛ ተቋሞቻቸው የተገባውን ደረጃ ሰጥተው እንዲማሩ የሚያደርጉት። የአጤ ጀርመን የመዳህኒት ቅመማ ከኢትዮጵያዊው የፈውስ መጸሐፍ ልቅናም ይቀዳል። የራሳቸውን የሚያከብሩት ጀርመኖች፤ የዕውቀት ዘርፍን በድንበር ወይንም በዞግ ሳይከልሉ ነፃነቱን ዓውጀውለታል። ይባረኩ። አሜን።   ማህበረ አያ እከሌወቼ የተፈጠሩበትን ዝሃ - ግራ፤ የተገኙበትን የእ...

#እንቁጣጣሽ።

ምስል
  #እንቁጣጣሽ ።   የማከብራችሁ ማህበረ ቅንነት፣ መጪው ዘመን የስኬት፣ የሰላም፣ የፍቅር እንዲሆንላችሁ እመኛለሁኝ። የእኔ ድንግል ጥበቃ አይለያችሁ። አሜን።   በተለይ ለኢትዮጵያ #እናቶች በሙሉ መጪው ዘመን #ከዕንባ #እርፍ የምትሉበት ዘመን ይሁንላችሁ። አሜን። በዱር በገደል፣ በእስር ቤት የምትገኙ ወገኖቼ አይዟችሁ። የእኔ ድንግል ጥበቃ አይለያችሁ። አሜን። ሁላችሁንም እመቤቴ ትጠብቅልኝ። አሜን።    ቅድስት አገር #ኢትዮጵያን ፣ ቅድስት አገር #ሲዊዘርላንድን ፣ ዓለማችን እግዚአብሄር አምላክ ሰላም ያድርግልኝ። አሜን። አዲስ ዓመት እየመጣ ዋዜማ ላይ ነን። አገር ቤት በተለይ ጎንደር ዋዜማው ላይ ልዩ ሥርዓት አለ። ያ ይናፍቀኛል። ማምሻ ላይ በግ፣ ዶሮ እየጮኽ፣ ቡና ተፈልቶ፣ አበባ ቆሎ እና ኑግ ተዘጋጅቶ ዳቦ ቀርቦ ልዩ የሆነች ፍቅር የሆነች የቤተሰብ አባል፣ ወይንም ወዳጅ ቡና ታፈላለች። ያ ድባብ እጅግ ይናፍቀኛል።   አዱኛወቼ ምዕራፍ ፲፮ በዚኽው ይከወናል። ከሁሉም ምዕራፎች አጭሩ ምዕራፍ ፲፮ ነው። ምክንያቴ አዲስ ዘመን በሩን ነገ ይከፍታል። በተጨማሪም አጤ አባይም ትልቅ ግሎባል ክስተት ነው። ስለሆነም ምዕራፍ ፲፮ ማጠናቀቅ ይገባዋል።   በመጪው ጥቂት ቀናት ምዕራፍ ፲፯ እጀምራለሁኝ። ተከባብረን የምንደማመጥበት የጨመተ ጊዜ እንዲሆንልን አምላኬን አላህን በርከክ ብየ እለምናለሁኝ። ኑሩልኝ። አሜን።   "አቤቱ #ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን። ጎዳናችን ንጹህ ልብ እንዲመራው ብንፈቅድ ተራራ የሚያክለውን ጥቅል የፈተና #ቱቦ መቋቋም ያስችለናል አምላካችን። እስኪ ደፍረን እንሞክረው።    ለቅኑ ጨዋ የኢትዮጵያ ህዝብ፣ ለብሩሁ አዲስ ትውልድ ሲባል ቅን፣ ንጹህ፣ ሩህሩህ፣ አ...

#በኖኽ #መርከቡ የአባይ ብሥራታዊ ዕጹብ ብራንድ ትልም ፍፃሜ እንኳን ደስ አለሽ ልዕልት ኢትዮጵያ! በልጆችሽ የተግባር ልዕልና #ልዩው #ብራንድሽ ለወግ በቃልሽ! !#እሰይ! ዛሬ ለእኔ ዕንቁ #ብሄራዊ ቀኔ ነው።

ምስል
  #በኖኽ #መርከቡ የአባይ ብሥራታዊ ዕጹብ ብራንድ ትልም ፍፃሜ እንኳን ደስ አለሽ ልዕልት ኢትዮጵያ! በልጆችሽ የተግባር ልዕልና #ልዩው #ብራንድሽ ለወግ በቃልሽ! ! #እሰይ ! ዛሬ ለእኔ ዕንቁ #ብሄራዊ ቀኔ ነው።   "አድርገህልኛል እና አመሰግንሃለሁ።"         ዘለግ ያለ ጹሁፍ ነው። ለቅጽበታውያን ሳይሆን የተረጋጋ፤ የጨመተ መንፈስ ለተመረቀላቸው፤ የትውልድ ጉዳይ ህሊናቸው ለሆነ ቅኖቼ የተፃፈ ማስታወሻ ነው። አመሰግናለሁኝ ጊዚያቸውን ለእኔ ለሚሸልሙ አዱኛወቼ።    #መርኃች ሆነ መሪያችን የዕውነት ተፈጥሮ ይሆን ዘንድ እንፍቀድ። ትሁታዊ ልመናዬ።   ይህ ከደስታ በላይ ሐሤት ነው። ከምድር እስከ አርያም ፍጹም የሆነ ልዩ ቅዱስ መንፈስን የሚመግብ። የሰው ልጅ አለሁ፤ እየኖርኩ ነው ማለት የሚችለው ዕውነትን #የማይፈራ ሲሆን ብቻ ነው። ዕውነት ለቤት እና ለዱር እንሰሳት - አልተፈጠረም። ዕውነት ለጋራ ሸንተረሩ - አልተፈጠረም፤ ዕውነት ለወንዝ ፏፏቴ - አልተፈጠረም። ዕውነት ለዝናብ - አልተፈጠረም።    ዕውነት ለወጀብም - አልተፈጠረም። ዕውነትበዕውነትነት የተፈጠረው የሰው ልጅ እንዲኖርበት ነው። ዕውነት የሆነውን ዕውነት፤ ሃሰት የሆነውን ደግሞ ሃሰት ማለት ይገባል። በዘመናችን ታላቅ የተግባር ተጋሎ ለስኬት ሲበቃ የእኔ ማለት ይገባል። ሊቀ ትጉኃንን ለማመስገን ቆጥቋጣ ልንሆን አይገባም።   #ኢትዮጵያዊነት ሜዳ በቀል አይደለም! ኢትዮጵያዊነት የእዳሪ ግኝትም አይደለም። የዊዝደም እንጂ።   ኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት መሥራችነቷ፦ ኢትዮጵያ የዓለም አንድነት ከመሠረቱ ቀዳሚ አገሮች መመደቧ፤ ኢትዮጵያ የቀጥታ ቅኝ ግዛትን፤ የእጅ አዙር ቅኝ ተገዥነትን...