ልጥፎች

የአደራ እጬጌ! የውል አሥራት! የኪዳን መሆን!

ምስል
ዬውጫሌ ውል አንቀጽ 17 ሳቢያ ነበርን?!?       ባድመስ አህጉር ነበረችን!?!   „ዬቅንነት፡ ቃል፡ እንዴት፡ ኃይለኛ፡ ነው!“ ( መጸሐፈ እዮብ ምዕራፍ ፮ ቁጥር ፳፭) ከሥርጉተ© ሥላሴ (Sergute©Selassie) ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ።  የአደራ እጬጌ! የውል አሥራት! የኪዳን መሆን! ·       እፍታ። ጤና ይስጥልኝ የ እኔዎቹ እንዴት ናችሁ? ደህና ናችሁ ወይ። ይህ ደግሞ December 16, 2016 በፈረንጆቹ ቀን የተጻፈ ነው። ሦስት ቀን ይቀረዋል ሁለት ዓመት ሊሞላው ማለት ነው። ይህን ጹሑፍ የጻፍኩት የጎንደር የህልውና የማንነት ተጋድሎ ሳቢያ ነው ስላሉ  የኢሳት እና የግንቦት 7 መንፈስ ደጋፊ ሊቃንት ስላሉ ነበር። እኔ በብዙ ሰው ብዙም አይገረመኝም። እምገረመው ግን በጸሐፊ አቶ ኤርምያስ ለገሰ ብቻ ነው። እሱ በወያኔ ሃርነት ትግራይ አዋራ ፓርቲ ሥር ይመራ በነበረው በኢህአዴግ ውስጥ የሎጅስቲክስ ሠራተኛ ሳይሆን መደበኛ የፖለቲካ ሠራተኛ ነው የነበረው። ለዛውም መምህር። በዛ ሙት መሬት ላለ ዶግማ ትውልድን ማህበረሰብን መቅረጽ። ስለዚህ እሱ የሳቢያ እና የምክንያትን ንጥረ ነገር በስማ በለው ሳይሆን በእውቅት መሬት ላይ ሰርቶበታል ኑሮበታል። የሞገድ ፖለቲከኛ አይደለም። ነገር ግን ኤንም ቢንም እንዳይከፋው ሆነ እና ያ ገናና የአማራ ተጋድሎ በሳቢያ ተጥቅልሎ አረፈ። ይህ ሲገርመኝ አነ ዶር ለማ መገርሳ ወደፊት ሲመጡ አብሶ ዶር አብይ አህመድ ሲመጡ ሌላ ሰብዕና ይዞ ነበር የመጣው። በቃ እማናውቅው ሰው ነበር የሆነው። እውነትን ለመወገነ ቅድመ ሁኔታ አያስፈለግም ነበር ለ አንድ በፖለቲካ ድርጅት ውስጥ መሬት ላይ ላለ ሰብዕና። ለወደፊትም ሚዛን ፋክት ቢሆን ነው ሰብዕናን አጽንቶ የሚያዘልቀው። የ