ልጥፎች

ከማርች 28, 2019 ልጥፎች በማሳየት ላይ

እርፍ! እልልልል ይታከል … እውነት ስለተሞሸረች …

ምስል
እርፍ! እልልልል ይታከል … እውነት ስለተሞሸረች … „በውን ጠበብ አትጮኽምን?“  ምዕራፍ ፰ ቁጥር  ፩ መፅሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 28.03.2019 ከእመ ዝምታ ሲዊዘርላንድ። የራስ ነገር ከሌለ በዬዘመኑ እንዲህ ነው! ቅልውጥ! ሚሊዮን ልጅን መንፈስ ጎዳና ተዳደሪ ማድረግ! ·        ተህሊና ትቀምጥ ይህቺ ወግ! https://www.satenaw.com/amharic/archives/65560 ዶ / ር   ብርሃኑ፤   ኦዲፒ   እና   አዴፓ  ( ሚኪይ   አምሃራ ) ኢንጂነር ታከለ ኡማ አዲስ ፕሮፖጋንዲስት አገኙ …በነጣ … ዙፋናቸውን ተሸካሚም አገኙ በብላሽ!  እንግዲህ ለኢንጀነሩ ቀይ ምንጣፍ ይጉዙላቸው… ሲያጋጥም የግንብ ጉድጓድ አርቲቡርቲ ግጥም! ዋው¡ፍቅሩ ደርቷል በአማራ ላይ ተዶልቷል!  አክ! እንትፍም በቀናቀኑ ተበጅቷል! የሰንበቱ ግርግር ከባህርዳር ከዚህ ጋር ይታይ የእጃችን አውጣን የሜንጫና የክላሽን ሸበላ … ሚዛን የማስጠበቅ ትውና … ብአዴንን የማሰጣት ድርማ … ፐፐፐፐፐፐፐፐፐ https://www.satenaw.com/amharic/archives/65690 ባለአደራ ምናምን የሚባለው ነገር ለኔ ትክክል አይመስለኝም ” ፕ / ር ብርሃኑ ነ ጋ March 28, 2019 << ባለአደራ ምናምን የሚባለው ነገር ለኔ ትክክል አይመስለኝም። አቶ ታከለ ይሄን የማሸጋገር ሂደት በሚመለከት በትክክል ያልሰራው ነገር አለ ከተባለ ሂስ ማቅረብ ጥሩ ነው። >> ፕ / ር ብርሃኑ ነጋ ምን ሲነጋ ማን ሲያነጋ ጨለማ ሲያወጋ ቀጥሎ ሊያዋጋ ለዚህ ነበር በሂልተን ሆቴ

ዕውነት ላይ ያለመቆም ችግር የትውልድ ብክነት ፋፍሪካ።

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ  „ከአፌ ቃል ፈቀቅ አትበል፤ አትዋትት፤ ትደግፍህምአለች። ውደዳት ትጠቅምህምአለች። ጥበብ ዓይነተኛ ነገር ናትና  ጥበብን አግኝ። ከሃብትህም ሁሉ ማስተዋልን አትርፍ“ መጽሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ ፬ ቁጥር ከ፭ እስከ ፯ ዕውነት ላይ ያለመቆም ችግር የትውልድ ብክነት ፋፍሪካ። ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 28.03.2019 ከእመ ዝምታ ሲዊዘርላንድ። ጤና ይስጥልኝ ውዶቼ እንዴት ናችሁ ደህና ናችሁ ወይ? ዛሬ ፏ ብላለች ልዕልት ጠሐይ። አላዛሯ ኢትዮጵያስ? በዘመናት መካከል የጠፋው፤ የከሰለው፤ የባከነው ትውልድ የሊሂቃኑ ዕውነት ላይ ያለመቆም ችግር ነው ብዬ አምናለሁኝ።   አብሶ ከራስ ተሰማ ናዳው የሴራ ፖለቲካ ማግስት ይህን መሰሉን ሴራ ውርስ ቅርስ በማድረግ ፖለቲከኞች ሲጠቀሙበት ትውልድ በጎራ ተለያይቶ የሳት ራት ሆኗል። ታጭዷል። ፈልሷል። ተጎርዷልም። አሁንም ዘልቋል መከታከቱ። ስለምን? ሴራ የዲያብሎስ ስለሆነ ከፈጣሪ አምላኩም ጋር ስለተለያዬ መንፈሱ። ፈጣሪ እፍ ብሎ መርቆ ከፈጠራቸው ጥባበት ጋርም ተፋልሷል የሊሂቃኑ ምህንድስና ። ማህከነ! ትውልድን በማበርከት የስካንድንብያ አገሮች እና ሲዊዘርላንድ የኢትዮጵያን ያህል የቀደመ የሊቃናት ሰማይ እና ምድርን የመረዳት ጥበብ ቢኖራቸው ከአሁኑ የበለጠ ሰውኛ ያልሆነ መንፈስኛ የሆነ ምጥቀት በተገኘባቸው ነበር።  ለእነሱ ስክነቱን ሲሰጥ ጥበብ ደግሞ ለኢትዮጵያ ተስጥቶ ባልተገናኝቶ እኟ አረንቋ ላይ እንገኛለን። እነሱ የሰላምም የስክነትም የስልጣኔ ባለቤት ናቸው ዛሬ። እኛ ደግሞ ካለንበት ከነበርንበት ወርድን ከእንሰሳትም ዝቅ ብለን ተ ፈጥሮን እና የሰው አፈጣጥርን ስንታገል እንገኛለን። ውሻ እንኳን ከለመደ በሆዋላ ለለደመደ