ልጥፎች

ከኦገስት 7, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ነሐሴ አንድ ቀን ስተራሳት አንተን ገድለኸዋል።

ምስል
ሰማዕትነት ያፈራው እሸታዊ ማንነት። „እንደዚሁ ሁሉ እግዚአብሄር የዘራቸው ነፍሳት ፈጥነው ይነሣሉ፤ እሱ ሰውን በውነቱ ካለመኖር ወደ መኖር አምጥቶ ፈጥሮታልና፤ በምታድን ቃሉ ፈጥኖ ያስነሣቸዋል፤ ማስነሣቱን አያዘገይም።““ መቃብያ ቀዳሚዊ ምዕራፍ ፲ ቁጥር ፮ ከሥርጉተ©ሥላሴ 07.08.2018 ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ ገድለ አማራ በባህርዳር ደም የተገበረበት የአማራ የማንነት ታአገድሎ ዕሴት! አማራ የግፍ ቀንበሩን በበቃኝ ታገድሎውን አህዱ ያለበት የሀምሌ 5ቱ 24ቱ ተጋድሎ ጎጃምን በቅኔያዊ ደሙ አንድ ያደረገበት ዕለት ነው ነሃሴ 1 ቀን። እንሆነ የተጋድሎው የህዝበ ውሳኔ ዕወጃ ሰነድ በደም ማህተም የተዘከረበት የደም ዋጋ ቀን። „እሱ ሰውን በውነቱ ካለመኖር ወደ መኖር አምጥቶ ፈጥሮታልና፤ በምታድን ቃሉ ፈጥኖ ያስነሣቸዋል፤ ማስነሣቱን አያዘገይም።“ የማዳን መለከት ከእዮር የተላከልን ሰሞናት ነበር ከሀምሌ 5 አስከ ነሀሴ አንድ 2008 ድረስ ያለው።   ዕሴታዊ የደም ግብር የድንጋጌ ዕለት መስከረም 1 ቀን። ትንግርት በደም ቀልሞ ተጋድሎው ጽናዊታዊ ድልድይ የተዘረጋበት ቀን ነበር ነሃሴ 1 ቀን 2008። ይህ ቀን ለአማራነት ፍጹም ልዩ ቅዱስ ቀኑ ነው። ሰማዕትነት ፈቅደው ሲቀበሉት ግብሩ በቅሎ - ጸድቆ - አስበሎ እንዲገኝ ቃል ኪዳን የሚታደስበት ስለሆነ "የበሉበት ወጪት ሰባሪ ላለመሆን" የተግባር ቋጠሮን በቆረጠ እና በወሰነ አቋም ለማዝለቅ ውል ከእነዚያ 76 ሰማዕታት ጋር ጎሎጎታን የምናስብበት፤ ቃላቸውን ብንበላ፤ ኪዳናቸውን ብናፈርስ በቁማችን እንፈርስ ዘንድ እምንወሰንበት እለት ነው።  ሰማዕቱን ማሳብ ብቻ ሳይሆን ዕውን የታገድሎው ዓላማ ገብቶን ከሆን በህይወት ያሉትን ጀግኖቻችን ድምጻቸውን

ግን እባክህን አትገንግን? 80 ችግር እንደገና ግን?

ምስል
ችግር በራሷ ላይ መጫን የለመደባት አላዛሯ ኢትዮጵያ 80 ችግርን ለዘለቄታ ፈቀደች። „አንተ የዘራኸው ዘር አይበቅልም ትላለህን፤  አንተ የዘራኸው ዘር ስንኳ ይበቅላል።“ መቃብያ ቀዳማዊ ምዕራፍ ፲ ቁጥር ፭። ከሥርጉተ ©ሥላሴ  07.08.2018 ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ። ·       ው ዶቼ … የኔዎቹ ማንም የዛሬውን ተደሞዬን አስተውሎት አልሰጠውም። ግን ደህና ናችሁን ውዶቼ? በሰሞናቱ  በሌሎች ጉዳዮች ተወጬ ነው እንጂ እጅግ በጥሞና የተከታተልኩት ዜና ነበር ባፈው ሳምንት … ያው ባነሩ ላይ ተለጥፎ ነው ያነብኩት ...  ውዶቼ ሰምታችኋዋል አይደለም ዛሬ በዚህ „ ኢትዮጵያዊነት ሱስ ነው“ ዘመን አዲስ ሌላ ፈተናም መደገኑን። "የኦሮሞ ተማሪዎች ማህበር ተሰመረተ" የሚል ዜና አንብቤያለሁኝ። የኖረው የ43 ዓመቱን ዳገት መውጣት ተስኖን ሌላ አዲስ መከራ ደግሞ እዬበቀለ ነው።  በሌላ ፎርም እና ይዘት። ነገ የአማራ፤ የትግሬ፤ የጉራጌ፤ የወላይታ፤ የኮንሶ፤ የኩናማ፤  ከንባታ፤ የሃድያ፤ የአፈር፤ የሀረሬ ወዘተ 80 የተማሪዎች ማህበር ደግሞ ይመሠረታል። ይህ ለምን ተፈለገ የሚለው ራሱን የቻለ አምክንዮ ነው። የኦሮሞ ተማሪዎች ማህበር ከመፍጠር ይልቅ የኢትዮጵያ ተማሪዎች ማህበር መፍጠር የተሻለ ነበር። ይህም ቢሆን አስፈላጊ አይደለም። የመማር ዕድል የሌላቸውን ወጣቶች አግላይ ነው። ጨቋኝ ነው። በዚህ መሥመርም ነው የኢህአፓ፤ የሻብያ፤ የወያኔ፤ የመኢሶን፤ የደርግ ሁሉም መከራ የመጣው። ያን ዛሬ ላይ እንድገመው ደግሞ ተብሏል። ·       ግ ርም በግራሞት። ስለምን ይሆን „የኦሮሞ ተማሪዎች ማህበር“ ምሥረታ ዛሬ አስፈላጊ የሆነው ይሆን? ወደ ኢትዮጵያዊነት ለመምጣት ያቀተው