ልጥፎች

ከሴፕቴምበር 10, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ኦ! አብይ እንኳንም የእኛ ሆንክልን!

ምስል
ለብጹዕን አቨው ይስሃቅን አማኑኤል ሰጣቸው። „ጻድቃን ሆይ በእግዚአብሄር ደስ ይበላችሁ፤           ለቅኖች ምስጋና ይገባል።“    መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ ፴፪ ቁጥር ፩ ከሥርጉተ©ሥላሴ 10.09.2018 ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ።                                                   ኑሩልን!                                   "በስም አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አህዱ አምላክ፤                            አሜን!" ሳይገባኝ እና ሳልመቼው  የደጀሰላሙን  ታምራት እናገር  ዘንድ ተገደድኩኝ። „ያዬነውን እንናገራለን የሰማነው እንመሰክራነን።“ እንዲሉ፡፡ ·          መነሻዬ። https://www.youtube.com/watch?v=_O_sP971z3k ጠ / ሚ ዶ / ር አብይ አህመድ ለብጹዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሪዎስ የመኖሪያ ቤት ቁልፍ አስረከቡ ይላል ፋና ቴሌቪዥን ያገኘሁት ዘገባ። ትናንት በጨርፍታ ነበር ዛሬ ዘለግ አድርጌ ደጋግሜ አዳመጥኩት። መቼም ዘንድሮ የምሥራች ይሁን መንፈሳችሁ ብሏል መዳህኒተ ዓለም ክርስቶስ። „አቤቱ በፈቃድህ ለሕይወቴ ሃይልን  ሰጠሃት ፊትህን መለስህ፤ እኔም ደነገጥሁ።“ የኔዎቹ ባለፈው የብጹዑ ወቅዱስ አባታችን አቡነ መርቆርዮስ  30ኛ ዓመት የፕትርክና የሲመት ባዕል ሲከበር ከፍቶኝ ነበር። ደረጃውን የጠበቀ አልነበረም። አያይዤም የብጹዑ ወቅዱስ አባታችን 4ኛ ፓትርያርከ  ዘኢትዮጵያ ቤት እጅግ ጠባብ እና ጥብቆ እንደሆነም ጠ/ ሚር አብይ ሊጎበኟቸው በሄዱ ጊዜ ታዝቤ ስለነበር ቅሬታዬንም አያይዤ ጽፌ ነበር። የልብን መሻት ያዬ ኤ

ለቀንበጥ ብሎግ ውዶቼ እንኳን አደረሳችሁ! መልካም አውድዓመት!

ምስል
ይድረስ ለቀንብጥ ብሎግ ታማኝ ታዳሚዎቼ በሙሉ። ከሥርጉተ ሥላሴ የቀንበጥ ብሎግና የፍቅራዊነት ዩቱብ አዘጋጅ። „ልባችሁ የቀና ሁላችሁም እልል በሉ።“  መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ ፴፩ ቁጥር ፲፩ ናፍቆቶቼ ሆይ! በቅድሚያ ዘመኑ ለተለወጠበት ምክንያታዊ መስዋዕትነትን ለከፈሉ ወገኖቻችን የህሊና ጸሎት በዬቤታችን እናደርስ ዘንድ እለምናችሁ አለሁኝ፤ ለሰኔ 16 ሰማዕታትንም አስበን። በዚህ እንስማማ። ቄሮ እና የአማራ የህልውና የማንነት ተጋድሎ ላደረጉት የሰፋ እና የደረጀ የተጋድሎ አውራነት፤ ለፍሬም መብቃት ሁሉ ምስጋና ይገባቸዋል። ለዚህ ተጋድሎ ግንባራቸውን ለባሩድ ለተሰዉት ነፍሳቸውን አርያም ገነት ያግባልን፤ አካላቸው ለጎደሉትም መጽናናቱን ይስጥልኝ። ቤተሰቦቻቸውንም ይጠብቅልን፤ አሜን! ጤና ይስጥልኝ እጅግ የማከብራችሁ እና ሙሉ መንፈሴን ለምልገሳችሁ የኔዎቹ፤ የብቻዬ የቀንበጥ ብሎግ ታዳሚዎች ሚስጢረኞቼ። እንዴት አላችሁልኝ? እንኳን ለዘመን መለወጫ ለ2011 ለቅዱስ ዮሖንስ ዋዜማ ዕለት አደረሳችሁ አደረስን። እንቡጢጣ መረጃ ስለ ጎንደር አለችኝ። እንዲህ አንድ የተለዬ ባህል አለው - ጎንደር። እርግጥ ከቤተሰብ ቤተሰብ ይለያያል አፈጸጻሙ። ለጎንደር ዋዜማው ፍጹም የተለዬ ግርማ ሞገስ አለው። እንዲያውም ዕለቱ የልጆች ሲሆን ዋዜማው ምሽት ላይ  የአዋቂዎች ነው ብል ያምርብኛል። ዋዜማው ምሽት ላይ ጉዝጓዙ ግጥም ብሎ ይጎዘጎዛል። በጉዝጓዙ ልክ አድዮ አለበት። ከዛ ቤተሰብ ክብ ሠርቶ አዲሱን ልብ ለብሶ፤ ያልገዛውም ጸዳ ያለውን መርጦ በረድፍ በረድፉ እንደ ዕድሜ ደረጃ ይቀመጣል።  ለቤተሰቡ ልዩ ሆና የምትወደድ የቅርብ ሰው ጎረቤት ልትሆን ትችላለች፤ አበልጅ ልትሆን ትችላለች፤ ጓደኛ ልትሆን ትችላለች፤ ምራት