ኦ! አብይ እንኳንም የእኛ ሆንክልን!
ለብጹዕን አቨው ይስሃቅን አማኑኤል ሰጣቸው። „ጻድቃን ሆይ በእግዚአብሄር ደስ ይበላችሁ፤ ለቅኖች ምስጋና ይገባል።“ መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ ፴፪ ቁጥር ፩ ከሥርጉተ©ሥላሴ 10.09.2018 ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ። ኑሩልን! "በስም አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አህዱ አምላክ፤ አሜን!" ሳይገባኝ እና ሳልመቼው የደጀሰላሙን ታምራት እናገር ዘንድ ተገደድኩኝ። „ያዬነውን እንናገራለን የሰማነው እንመሰክራነን።“ እንዲሉ፡፡ · መነሻዬ። https://www.youtube.com/watch?v=_O_sP971z3k ጠ / ሚ ዶ / ር አብይ አህመድ ለብጹዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሪዎስ የመኖሪያ ቤት ቁልፍ አስረከቡ ይላል ፋና ቴሌቪዥን ያገኘሁት ዘገባ። ትናንት በጨርፍታ ነበር ዛሬ ዘለግ አድርጌ ደጋግሜ አዳመጥኩት። መቼም ዘንድሮ የምሥራች ይሁን መንፈሳችሁ ብሏል መዳህኒተ ዓለም ክርስቶስ። „አቤቱ በፈቃድህ ለሕይወቴ ሃይልን ሰጠሃት ፊትህን መለስህ፤ እኔም ደነገጥሁ።“ የኔዎቹ ባለፈው የብጹዑ ወቅዱስ አባታችን አቡነ መርቆርዮስ 30ኛ ዓመት የፕትርክና የሲመት ባዕል ሲከበር ከፍቶኝ ነበር። ደረጃውን የጠበቀ አልነበረም። አያይዤም የብጹዑ ወቅዱስ አባታችን 4ኛ ፓትርያርከ ዘኢትዮጵያ ቤት እጅግ ጠባብ እና ጥብቆ እንደሆነም ጠ/ ሚር አብይ ሊጎበኟቸው በሄዱ ጊዜ ታዝቤ ስለነበር ቅሬታዬንም አያይዤ ጽፌ ነበር። የልብን መሻት ያዬ ኤ