ልጥፎች

ከዲሴምበር 26, 2023 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ይድረስ ለኢትዮጵያ አገራዊ የምክክር ኮሚሽን። ኢትዮጵያ - አዲስ አበባ።

ምስል
  ይድረስ ለኢትዮጵያ አገራዊ የምክክር ኮሚሽን። ኢትዮጵያ - አዲስ አበባ። "እግዚአብሄር በአንድም በሌላም ይናገራል ሰው ግን አያስተውለውም" የኢትዮጵያ አገራዊ የምክክር ኮሚሽን ለማን እና ስለማን ይሆን የተቋቋመው??? #ስለአለቅትነት ይሆን??? አነሳችሁብኝ። እንደምን ሙሁራን ለሚያቀርቡትገንቢዕይታ ዕውቅና መስጠት ተሳናችሁ???? #ቁስለት ! የተከበሩ ፕሮፌሰር ሚንጋ ነጋሽ ከአደባባይ ሚዲያ ጋር ያደረጉትን ቃለ ምልልስ በጥሞና ለአራት ጊዜ ያህል አዳመጥኩት። አምስተኛውም ለአዲሱ ዓመት ተቀጥሯል። አይጠገብም። ተቋም ነው። የአወያዩ የአቶ አቤል ጋሹ የአጠያዬቅ ዘዬም ለፕሮፌሰር ሚንጋ ሜጋ አቅም ደረጃውን የጠበቀ ሆኖ አግኝቼዋለሁኝ። በዚህ ዓመት በመቆጠብካዳመጥኳቸው ቃለ ምልልሶች ቀንዲሉ ሆኖልኛል ለእኔ። የኢትዮጵያን ክብረት እና አዱኛም ፏ ብሎ ያዬሁበት አጋጣሚ ነበር ማለት እችላለሁኝ። መስጦኛል። ተደምሜበታለሁኝ። ውስጤንም አግኝቸበታለሁኝ። ፕሮፖጋንዲስት ለማያስፈልገን ኢትዮጵያዊ ዜጎች ልካችን አግኝተናል ብዬ አስባለሁኝ። ለዚህም ነው እኔ ኢትዮጵያን በተፈጥሯዋ ልክ ያነበቡ፤ የተረጎሙ እና ያመሳጠሩ ከሳይለንት ማጆሪቲ ውስጥ ያሉ በቲም ፈላስፊቷን አገሬን ይመሩ ዘንድ ዕድሉን እንዲያገኙ እምመኜውም። ፌስ ቡኬ ላይ ለሁለተኛ ጊዜ ነው ሼር የማደርገው። ባሉኝ ሁሉ ሚዲያወቼም ብሎጌን ጨምሮ ሼር አድርጌዋለሁኝ። ከማህበራዊ ሚዲያ ርቀው ለሚኖሩ ወገኖቼም ሼር አድርጌዋለሁኝ። የጠራ አቅጣጫ ያለው ብቻ ሳይሆን አብዝቶ ቅንነትን ማዕረጉ ያደረገ መሰጠትን ስለአገኜሁበት። የጨመተ እና የሰከነ፤ እላፊ ያልሄደ ጠፈፍ ያለ የእኛነት የኔታነትን አይቸበታለሁኝ። መስታውትም ራዲዮሎጂም ማለት እችላለሁኝ። በፍፁም ሁኔታ የገረመኝ ደግሞ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ህይወቴ ከልጅነት እስ

ለምን ሥማችሁን #አብይ አትሉትም? ጓዘ ቀላል ጥያቄ ለፋና፤ ለዋልታ፤ ለኢትዮጵያ ቴሌቪዥን እና ራዲዮ፤ #ለኦሚኮ።

ምስል
  ለምን ሥማችሁን #አብይ አትሉትም? ጓዘ ቀላል ጥያቄ ለፋና፤ ለዋልታ፤ ለኢትዮጵያ ቴሌቪዥን እና ራዲዮ፤ #ለኦሚኮ ። ኢትዮጵያ አዲስ አበባ። "እግዚአብሄር በአንድም በሌላም ይናገራል ሰው ግን አያስተውለውም።"     እንዴት ናችሁ ማህበረሚዲያወች። የማንእንበላችሁ? የማንስ ትሰኛላችሁ? መቼ ይሆን ለገባችሁት ሙያዊ ቃል ሟች ሆናችሁ የምትገኙት? ዘወትር አንጋችነት አይሰለቻችሁም? ግን ስለምንሥማችሁን አብይ አትሉትም።መሃያ ቆርጠው የሚያስተዳድሧችሁ ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ አሊ ናቸውን? በቃ የሳቸው ውሎ አዳር ዘጋቢ ብቻ ሁናችሁ ቀራችሁ እኮ? ግን የቀራችሁንስ መቼ ታስደምጡን ይሆን? የሌሊቱን አዳርንም፤ የጠሎት ሥርዓቱን ሁለመናውን ልጠቅሰው የማልሻውን ሁሉ? እሳቸውም እኮ እንደ እናንተ ኢትዮጵያ ቀጥራ የምታስተዳድራቸው አገልጋይ እንጂ አሰሪያችሁ አይደሉም። ይህንያክልግልምት ብሎን እስኪያቅለሸልሸንድረስ ዝክረ እሳቸው ብቻ? ሥራጠፋን? የሚገርመኝስለ ራሺያ እና ዩክሬን፤ ስለ ፍልስጤም እና እስራኤልሐተታ አላችሁ። አንዳንድጊዜ ፋና፤ ዋልታ፤ ኢቲቢ፤ ጁቢተር ላይ ያላችሁ ይመስለኛል። በቃ የመጠቃችሁ። የደም አላባ፤ የዕንባ ጎርፍ፤ የድሮንሥልጣኔ በህዝብ፤ በቅርስ፤ በውርስ፤ በሃይማኖት፤ በትውልድ ላይቀንከሌት በጭካኔ እዬዘነበእናንተ የጠቅላይ ሚር አብይአህመድን ፋንታዚስታቆላምጡ፤ ስታሽሞነሙ ግንመሬት ላይ ስለመኖራችሁ ይረዳኛል። ለእኔ በኢትዮጵያ መከራ ላይ እያላገጠ፤ እዬተጫወተ ያለው እናአረመኔነት እንዲንሰራፋ፤ ትውልድ በባዕቱ፤ ትውልድ በሁለመናው ይነቀል ዘንድ እዬሠራችሁ ያላችሁ ሚሳኤሎች እናንተው ናችሁ። የጥፋት መልዕክተኝነትን ስለምን እንደምንትከባከቡ ይጨንቃል። ይጠባል። የኢትዮጵያ አምላክም ሩቅ ይመስላችኋል። የኢትዮጵያአምላክም የማይፈርድይመስላችቿል።