ልጥፎች

ከኤፕሪል 16, 2021 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ኢትዮጵያ ተምች ነው የወረደባት።

ምስል
  ·        ኢትዮጵያ ተምች ነው የወረደባት።   ዕለተ አርብ ማዕዶተ ኢትዮጵያ በከበቡሽ የቁራሽ እንጀራ ብራና በቢሆነኝ የተብራራ ብራ በሰብለ ሕይወት አዝመራ ለራህብ የሚራር። „ኃጣን ግን ዝም ብለው በጨለማ  ይቀመጣሉ፤  ሰው በኃይሉ አይበረታም“ (መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ ምዕራፍ 2 ቁጥር 9) ኢትዮጵያዊነትን ያከበረ፤ ያጸደቀ፤ ያሰበለ ለካቴና ሲሰጥ ኢትዮጵያ የት ነሽ ብሎ መጠዬቅ ይገባል። አወን ኢትዮጵያ ካቴና ላይ ናት። ለምን „በገዳ መደመር“ ስላልተካተተች። ይህን አሻም ያሉ ካቴና ላይ ናቸው። ወይንም በረጅም ገመድ በቁም እስር። እሺ ያሉ ደግሞ በከራባት እና በገበርዲን ሰርግ እና መልስ ላይ። ኬክም አለበት። ኢትዮጵያም ሙሉ ወርዱ ቀርቶባት ማቅ ለብሳ ትንፋሽ ባገኜች ምንኛ ዕድለኛ በሆነች ነበር። ህወሃት መራሹ ኢህዴግ የከታተፋት ኢትዮጵያ እንኳን አሁን የለችም። ድፍን ነገር። አቶ እስክንድር ነጋ ሲታሰር እኮ ነገሩ አብቅቷል። እ። ከዛ በፊት ኢንጂነር ስመኜው በቀለም ሲገደሉ የኢትዮጵያ ሉዕላዊነት ተረሽኗል። ነገረ አባይ እኮ ረግረግ ውስጥ የገባው ለዛ አሉታዊ ዴሞግራፊ የኮፒ ራይት ሽሚያ ላይ ሲዳካ ነበር። ግን ልብ መሸመቻ ይኖር ይሆን? እህ። ማፈላለጉ ይገባል ብዬ ነው። ገዳ አባይ የእኔ ነው አለ። ሊቃውንታቱ የፈለሰሙት፤ የመሩት፤ ያስተዳደሩት በእኔ ጠረን ነው ሲል ነበር አብይዝም ታላቁን ምስክር በአደባባይ በእርስ መዲናዋ ደመ ከልብ ያደረገው። የሄሮድስ መለስ ዜናዊን ፈጣራም በአደባባይ ነው የተዘረፈው። መስዋዕትነቱን እንደምን እንደ ተቀረደደ እራሱ ዘመን ይገልጠዋል። ዘመን ያብራራዋል። ተከድኖ፤ ተከርችሞ፤ የሚቀር ምንም ነገር የለም እና። ነገረ ኢትዮጵያ በሉት፤ ነገረ አፍሪካ ቀንድ፤ ነገረ መካከለኛው አፍሪካ መከራ

ጭቆና ሲናፍቅ።

ምስል
  ·        ጭቆና ሲናፍቅ። ዕለተ አርብ ማዕዶተ ኢትዮጵያ በከበቡሽ የቁራሽ እንጀራ ብራና በቢሆነኝ የተብራራ ብራ በሰብለ ሕይወት አዝመራ ለራህብ የሚራር። ·        „ሐና ወንድ ልጅ ወለደች እርስዋም ከእግዚአብሔር    ለምኜዋለሁ ስትል ሥሙን ሳሙኤል ብላ ጠራችው“      (መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ ምዕራፍ 1 ቁጥር 20)   ጭቆና ይናፍቃል። ጭቆናውም አልተፈቀደም። ሁለመናው ጉድጓድ ሆኗል። መፍትሄው እራሱ ታስሯል። መፍትሄው ታግዷል። ተስፋ እስር ላይ ነው። ድብልቅልቅ ላይ ነን። ሁሉ ነገር ተመሽጓል። ሁሉ ነገር ገደል ሆኗል። ዘመነ ፍዳ ነው። ዘመነ ምጻዕት ነው። ኢትዮጵያ ከፍቷቷል። ኢትዮጵያ አንገቷን ደፍታለች። ኢትዮጵያን ማሰብ አልቻልነም። ኢትዮጵያን ውስጥ ማድረግ አቅም አጣን።   ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 16.04.2021 ኦ! ኢትዮጵያ ሆይ ቀንሽ መቼ ይመጣ ይሆን? አሳዘንሽኝ።  

ፈሪነት …

ምስል
  ፈሪነት …   ዕለተ አርብ ማዕዶተ ኢትዮጵያ በከበቡሽ የቁራሽ እንጀራ ብራና በቢሆነኝ የተብራራ ብራ በሰብለ ሕይወት አዝመራ ለራህብ የሚራር። „ሐና ወንድ ልጅ ወለደች እርስዋም ከእግዚአብሔረ ለምኜዋለሁ ስትል ሥሙን ሳሙኤል ብላ ጠራችው“ (መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ ምዕራፍ 1 ቁጥር 20)   ቢያንስ የሃሳብ አቅም አምጦ መውለድ ይቻል ነበር። በተነው የተበተነ ለመሰብሰብ አሁንም ለብታ የለም። ሃሳብ ይፈራል። ሞጋች ይፈራል። ሃሳብ ሞጋች የሚፈራው ገዢው ብቻ አይደለም። በትብትብ ውስጥ ያለው፤ ያልነፃው፤ ያልደነገለው፤ ያልቆረጠው ሰብዕና ሁሉ ነው ሞጋች ሃሳብ የሚፈራው መድረኩ ያለው ደግሞ እሱ ነው። እንደ ድሪቱ ቢጣፍ፤ ቢደረት ችግሩ አፍጥጦ እዬገሰገሰ ነው። እዬዋጠ ነው። በዝምታ ውስጥ መክኖ መቅረትን የመሰለ መከራ የለም። መከራ። አወን መከራ። አገር እንደ ዋዛ? ሃይማኖት እንደ ዋዛ? የሰው ልጅ እንደ ዋዛ? ተፈጥሮ እንደ ዋዛ? ታሪክ እንደ ዋዘ? ትውፊት እንደ ዋዛ? ትሩፋት እንደ ዋዛ? ማግሥት እንደ ዋዛ? ትናንት እንደ ዋዛ? ዛሬም እንደ ዋዛ? የወዘኞች ዘመን? ሁላችንም ዋዘኞች ነን። ከዋዠኝነት የዳኑ ብጹዓን ናቸው እላለሁኝ። እኔው። እራሱ የኃይል አሰላልፉ ዝንቅ፤ ቅልቅል፤ ያለዬለት፤ አሳቻ፤ አሳሳችም ነው። እንደ እኔ ሌላው ይታዬው ይሆን አይታዬው አላውቅም። እኔ ግን እማዬው ተዛነፍ ነገር ነው። ሚዛን የሚአስጠብቁ፤ የሚያስክኑ፤ ስንፈላ እና ስንበርድ ሙቀቱን አስተካክሎ ሊመሩ፤ ሊያስተዳድሩ የሚችል ቅዱስ መንፈስ ያስፍለገናል። ያልባለቀ ንጹህ ሰብዕና ያስፈልገናል። እንጸልይ። እንጹም። እንስገድ። አንደበታችን እንረም። እራሳችን እንቅጣ። ትዕዛዝ አይደለም። ትህትናዊ ማሳሰቢያ እንጂ። ኢትዮጵያ ታሳዝነኛለች። እግዚአብሄር ይ

"ተረኝነት" ያደከመኝ አኞ ፖለቲካ ....

ምስል
    እንኳን ወደ ከበቡሽ ሚዲያ በሰላም መጡልኝ።  ተረኝነት ያደከመኝ አኞ ፖለቲካ ..  ዕለተ አርብ ማዕዶተ ኢትዮጵያ በከበቡሽ የቁራሽ እንጀራ ብራና በቢሆነኝ የተብራራ ብራ በሰብለ ሕይወት አዝመራ ለራህብ የሚራር። „ሐና ወንድ ልጅ ወለደች እርስዋም ከእግዚአብሔረ ለምኜዋለሁ ስትል ሥሙን ሳሙኤል ብላ ጠራችው“ (መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ ምዕራፍ 1 ቁጥር 20) ልብ - ኩላሊት - ሳንባ - ጉበት - አንጀት - ብቻቸውን ሆነው ሰውን መፍጠር ይችላሉን? ሰው ውህድ ነው። ኢትዮጵያም እንደዛው ናት። ተገጣጥማ አልተሠራችም። ተብትና አልተሰበሰበችም። ሂደቱ በጥበብ፤ በፈቃደ እግዚአብሄር በፈቃደ አለህ የተከወነ ነው። ይህን ሂደት ጥሶ፤ ይህን ሂደት ረግጦ ይህን የዘመና የሂደት ትረፉት ጨፍልቆ ኢትዮጵያን ልክ የጉልት ድንች የሚያደርግ ክፉ ሃሳብ፤ ክፉ ድርጊት በምድሪቱ ሰፍኗል። ከዚህ ክፉ ከሚመራው መንጦላዊት ሥርዓት ደግነት፤ መልካምነት ርህርህና አይወለደም። ታስታውሱ ከሆነ ደግነት ተሰደደ ብዬ ጽፌ ነበር። ደግነት ሲሰደድ ሰዋዊነትም፤ ተፈጥሯዊነትም ይሰደዳል። በደግነት የምትታወቀው እናት አገር ኢትዮጵያ እሱንም አሳጥተው አስፈሪ አደረጉት ሁለመናው። መከራው ተቃሎ „ተረኝነት“ ይባላል። እህ! „ተረኝነት?“ እም! „ተረኝነት“ ኦ! „ተረኝነት“ የሚሆነው ነገር ሁሉ ተራ ነውን? የሚሆነው ነገር በደዴ የሚከውን ነውን? የሚፈፀመው ሰቆቃ „ተረኝነት“ ይገልጸዋልን? ኢትዮጵያ እኮ በስውርም በግልጥም በባዕድ መንፈስ እጅ ወድቃለች። ሱባኤ፤ ድዋ፤ ንግግር፤ ውይይት፤ ምክክር ሁሉ ፈቃደ እግዚአብሔርን ይጠይቃል። አልሰከንም። አልረጋነም። በውስጣችን ያለው ክፉ ነገር ተሸክሞ ፈተናውን የመሸከም፤ መፍትሄ የማመንጨት አቅም እንደምን አምጠን መውለድ

ኢትዮጵያውያን አብይ ሠራሸ አይደለንም።

ምስል
   እንኳን ወደ ከበቡሽ ብሎግ በሰላም መጡልኝ።  ·        ኢትዮጵያውያን አብይ ሠራሸ አይደለንም።   ዕለተ አርብ ማዕዶተ ኢትዮጵያ በከበቡሽ የቁራሽ እንጀራ ብራና በቢሆነኝ የተብራራ ብራ በሰብለ ሕይወት አዝመራ ለራህብ የሚራር። „ሐና ወንድ ልጅ ወለደች እርስዋም ከእግዚአብሔረ ለምኜዋለሁ ስትል ሥሙን ሳሙኤል ብላ ጠራችው“ (መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ ምዕራፍ 1 ቁጥር 20 ) የፈጠረን እግዚአብሔር ነው። አገራችን ኢትዮጵያን የሰጠን አምላካችን ነው። እኛንም አገራችንም የፈጠረ አምላክ አለልን። ተስፋ እግዚአብሔር ነው። ተስፋም ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው። እግዚአብሔርን ተስፋ ማድረግ ይገባል። ኃያል አምላክ አለን። ተመስገን። ማህጸን አለኝ ሳይሉን ይቀራሉን ዶር አብይ አህመድ አሊ?   እኔ እንማስበው ሄሮድስ ጠቅላይ ሚኒስተር አብይ አህመድ የነገሥታቱን ታሪክ፤ የፀሐፍትን ታሪክ፤ የኢትዮጵያን ታሪክ እኔ ሠራሁት እያሉን ነው ያሉት። ከውስጥ ሆናችሁ ስታዩት። ኢትዮጵያንም እኔ ሠራኋት አይቀሬ ነው። እሱ ብቻ አይደለም አይድነቃችሁ የአብይዝም ትውልድ እንዳለ በህሊናቸው ዳንቴል ውስጥ ያምናሉ። እኛንም ጠፍጥፈው፤ አንቦልቡለው እንደ ቀረጹን ነው የሚያስቡት።   ለዚህ ነው ጋልበው ጋልበው እርገቱ ዲያስፖራው የሚሆነው። ሎቢስት ቅጠሩልኝ እኮ ከሰሞኑ ተደምጧል። ያን ጊዜ 100 ቀን ሳይሞላቸው ነበር ስሜን አሜሪካ ለመውጣት የተጣደፉት። ለምን ተጣደፉ ብሎ የጠዬቀ የለም? እሳቸው ያጎደሉት ነገር የለም። የጎደልነው እኛ ነን። ከሥር ሳይሆን ተንሳፈን የምንገኝ።   በሳቸው የኢማጅኔሽ ዓለም ነው ሁላችንም ታቁረን ያለነው። ግጭቱ ይህ ነው። ጦርነቱ ይህ ነው። ቆይተው ማህጸንም አለኝ ሊሉን

ጆሮ ያለው ዓይን ቢኖረን? መዳን በመዳፍ …

ምስል
  ·        ጆሮ ያለው ዓይን ቢኖረን? መዳን በመዳፍ … ዕለተ አርብ ማዕዶተ ኢትዮጵያ በከበቡሽ የቁራሽ እንጀራ ብራና በቢሆነኝ የተብራራ ብራ በሰብለ ሕይወት አዝመራ ለራህብ የሚራር። „ዝም ብዬ የመከራን ቀን እጠበቃለሁ።“ (ትንቢተ ዕንባቆም ምዕራፍ 3 ቁጥር 17 ) ·        ነገረ ኢትዮጵያ ቁልቁለት ሆኗል።   በውሳጧ ስለመኖራችን ግራ ሆኗል። ኢትዮጵያ ቀዝቅዟታል። ኢትዮጵያ በርዷታል። ኢትዮጵያ ከፍቷቷል። ኢትዮጵያ ጨልሞባታል። ዘመኑ እራሱ ምህላ ሊኖረው ይገባል። ህዝቡ ምህላ ሊያደርግ ይገባል። በዬለም ያለ ህዝብ በዬለም ለመኖርም አልተፈቀደለትም። ከቅንቶት ወጥቶ ውስጥን መፈተሽ ይጠይቃል። አንድ አቶ ልደቱ አያሌውን እንደ አንድ የምርምር ማዕከል አድርገን ብንወሰድ ትናንት የወደቅንበትን፤ ዛሬ እዬወደቅን ያለንበትን፤ ነገ የምንወድቅበትን አቅጣጫ፤ ጭብጥ፤ ፋክት ማዬት ይቻላል። ጆሮ ያለው ዓይን ቢኖረን።   እግዚአብሄር ይስጥልኝ። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 16.04.2021 ጎዳናዬ ለሥር ነቀል ለወጥ መታገል ነው።    

Bitte ….

ምስል
  „ Viele stehen wider mich auf, viel sagen von meiner Selle ፡ “ (Psalmen   3/2 ) … Bitte …. Ich will nicht denken Ich halt nichts davon Ich möchte nicht darüber nachdenken. So denke ich Ich habe nachgedacht Ich habe etwas überlegt Ich denke. Es kommt und stört mich Zuviel Denken ist nicht gesund Ich denke Stunde um Stunde Ich denke im Kreis Es dreht und dreht und drehte Ich will nicht sehnen Aber es kommt schnell. Ich will alleine bleiben Ich will andere sprechen Ich will allein beten Aber das geht es nicht Es kommt und stört mich … und ich vergessen meine Idee. Ich will allein gehen Ich will allein reisen Aber es kommt immer mit. Ich will allein leben Ich will allein essen Ich will allein schlafen Ich will allein sitzen Ich will es wegmachen Aber es ist wieder da Gegen mich. Ich mag es nicht Aber es liebt mich Bitte! mein Denke! Lass mich in Ruhe! Gib mir eine Ruhepause! Möge Gott die Welt und uns beschüt