ልጥፎች

ከማርች 26, 2019 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ድንግል ሆይ! ጋዜጠኛ አበበ ገላውን ጠብቂልን! አደራ!

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ  ድንግል ሆይ! ጋዜጠኛ አበበ ገላውን  ጠብቂልን! አደራ! „ኃጢያትን ተዋት እደ ልቦናህ አቅና፤ ልቦናህንም ከኃጢያት ሁሉ አንፃ“ ምዕራፍ ፴፰ ቁጥር ፭ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 26.03.2019 ከእመ ዝምታ። ጤና ይስጥልኝ ውዶቼ እንዴት ናችሁ? ደህና ናችሁ ወይ? የማይሰማ ነገር የለም። ሌላ ሰው ቢናገረው ምንም አይደንቀኝም።  አቶ ኤርምያስ ለገሰ በጸሐፊነትም፤ በም/ሚር ማዕረግም፤ በድርጅት አባልነትም የበቃ ተመክሮ ያለው ሰው ነው። መምህርም ነው። መምህር ሰብዕናው ለሁሉም አባትነት ይመስለኛል። አቨይ አባቴ እንደዛ ነበር። ነገር ግን ይህ ነገር ያዳመጥኩት አመክንዮ እሱን የሚገልጥ አልመስል አለኝ። ጋዜጠኛ አበበ ገላውን አሳልፎ የሚያሰጥ መረጃ ሜዳ ላይ ዘክዝኮታል። ዘርግፎታል። ሞትም ፈርዶበታል ያ ጥቃት ያወጣ ጋዜጠና። እጅግ ያስደነግጣል።   እንዴት ጓዱን አሳልፎ ይስጣል። ለዛውም በዚህ ቋያ ጊዜ። የኃይል አሰላለፉ ባልጠራበት ወቅት። ጓድን፤ ክፉ ደጉን አብሮ አሳልፎ፤ ጥቃትን ላወጣ ወንድም እንዴት በአደባባይ ሞት እንዲፈረድበት ይደረጋል። እያንዳንዱ ሰው እኮ ለራሱ ሰብዕና ጠንቃቃ ነው። ለዛውም ጠ/ሚር አብይ አህመድ አሁን እደማያቸው ከሆነ አይደለም ሰብዕናቸውን የሚንድ ትችትን እንኳን ለማስተናገድ የሚፈቅዱ አልሆነም። ጫን ያለ መከራ ከፊታችን ተደቅኗል። እንኳንስ ይህ በጠቅላላ በሥልጣናቸው የመጣ ጉዳይ ...  https://www.youtube.com/watch?v=0nWgC-QijJg ESAT Eletawi Part Two Mon 25 Mar 2019 1 ለመሆኑ ትውልድ የማይተካው ያ ትንታግ የጀግኖች ቁንጮ አንበሳ፤ የወንዶች ቀንዲል አሁን ጋዜጠኛ አበ

የወሎ ማህበር ምሥረታ የሴራው ሹርባ።

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ  የወሎ ማህበር ምሥረታ የሴራው ሹርባ። „ጥበብስ በቀደሙ ሰዎች ሁሉ ዘንድ ተመረመረች።“  መጽሐፈ ሲራክ ምዕራፍ ፴፱ ቁጥር ፩ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 26.03.2019 ከእመ ዝምታ። ·          መግቢያ ትናንት አንድ ጹሑፍ ጽፌ ነበር። የግንቦት 7 ስብሰባ በባህርዳር መስተጓጎል ሆን ተብሎ ታቅዶ እንደተከወነ ። የወሎ ማህበርም በተመሳሳይ ሁኔታ የተከወነ ነው። ታቅዶ ታልሞ። በአዲሱ የብአዴን አመራር ጫና ለመፍጠር ። ከኦነጋውያን የሜጫ ሱናሜ ጋር እኩል እንዲታይ ለማድረግ። የዚህ ቅንብር ባላንባራስ ደግሞ ጃዋርውያኑ አቶ ንጉሡ ጥላሁን ናቸው የሳቸው ኔት ነው ይህን ተግባር የሚየስከውነው። ክልሉን ማወክ ያስፈልጋል። የሜጫ ፖለቲካ በሁለት እግሩ ይቆም ዘንድ … የሳቸውም የቃልኪዳን ሰነድ ይዘልቅ ዘንድ። ·          ጉዳይ። የተከባራችሁ የጹሑፌ ታዳሚዎች ... በኢትዮጵያ የነበሩ 14 ክ/ አገሮች ነበሩ። እነዚህ 14 ክፍለ አገሮች በጣሊያን ትልም እሰፈፃሚ በኦነግ እና በህወሃት የወል ኮሶ ህገ መንግሥት ክልል በሚል ስያሜ በዛ ሥር ወድቀው ፍዳ እያስከፈሉ ነው። ዛሬ ጉዳዬ ይህ አይደለም። አማራ የሚባል ማህበረሰብ ከዬለም ጀምሮ ሰፊ የምንጠራ እርብርብ 50 ዓመት ሙሉ ተካሄዶበታል። ይህ ሥልጡን እና አስተዋይ ህዝብ ትቢያ ለብሶ ከመቃብር በታች መኖሩን የሚያልሙ እልፎች ናቸው። ጸረ ኢትዮጵያ የሆነ መንፈስ ሁሉ የዚህ ደቦ አባልተኛ ነው። እከሌ ተከሌ የለበትም። ስለሆነም አማራን ወጥ መንፈሱን ለመጻረር የማይደረግ ነገር የለም። ያው ዘር አልባ እንዲሆን ከጸደቀው ህገ መንግሥት ጀምሮ በፖሊሲ ደረጃ 27 ዓመት ተግባሩ በትጋት ቀጥሏል። እንሆ ዕድ