ልጥፎች

ከጁን 29, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ክፍል ሁለት ማጠቃለያ፤ ዓይነ ጠባብነት!

ምስል
ወጣቶች እንደ 66ቱ ዘመን ዓይነ ጠባቦች መሆን አይገባቸውም። ክፍል ሁለት ማጠቃለያ። ከሥርጉተ ሥላሴ 29.06.2018 (ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ)  „የወይን ጠጅ ፌዘኛ ያደርጋል፤ ብርቱ መጠጥም  ጠበኛ ያደርጋል፤  በዚህ የሳተ ሁሉ ጠቢብ አይደለም“  (መጽሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ ፳ ቁጥር ፩) ·       እፍታ ዛሬ ነው ከብራና ሳተናው የገባሁት። ትናንትና በተከታታይ የጻፍኳቸው የሰቆቃው አማራ ጉዳይ እና የእውነት ጠበቃ ማጣት በሚመለከት ስጽፍ ስለዋልኩኝ ጊዜ አልነበረኝም። ·       መነሻዬ። አሁን ዛሬ ሳተናው ብራና ላይ የኢሳቱ ጋዜጣኛ አቶ መሳይ መኮነን የመደመር ፖለቲካ አስፈርቶታል። „ ከዚህ አንዳንዶች ባይደመሩስ ?“ ( መሳይ መኮነን ) June 27, 2018 https://www.satenaw.com/amharic/archives/59493 „አንዳንዶችስ ባይደመሩ ይለናል?“  ትንታጉ ጋዜጠኛ። ጽዋው የማንፌሰቶ ማህበርተኝነት ነው። ሌላ ቁምነገር የለውም። መልካም ነገር ግን ብሄርም፤ ፖለቲካም፤ ማንፌስቶም የለውም። የሆነ ሆኖ የኔዎቹ ማጠቃለያው እንሆ። የይቅርታ ልብ ሳይኖረን ለውጥ ያማል። ንጹህ ልብ ሳይኖረን ኢትዮጵያዊነት ይጎመዝዛል። ኢትዮጵያ ሰፊ አገር ናት ሁሉንም እንደ አመሉ የመቻል አቅም ችሎታ ክህሎት አላት። ሰዎች በደከሙበት የመደመር ዕልፍኝም ቤተኛ እና ተርተኛ ይለይ ይከብዳል። ሁልጊዜ በ አጥር ተከልሎ ሁልጊዜ ቂምን ተጠልሎ ሁልጊዜ ቋስን እርሾ አድርጎ ተውልድን መገንባት ጋዳ ነው። የሚያውል የሚያሰድር የ አምክንዮ አቅም ጠፋ፤ አጅንዳ የለም መሼ ነጋ መብተክተክ … ·        ገመና። ይሄ ሁሉ ጓዝ ተይዞ ማህበረ ደራጎንን ማሸነፍ አይቻልም። ስንት

ዓይነ ጠባብነት?

ምስል
ወጣቶች እንደ 66ቱ ዘመን ዓይነ ጠባቦች መሆን አይገባቸውም። ክፍል አንድ። ከሥርጉተ ሥላሴ 29.06.2018 (ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ) „የጆሮ ጠቢብ ቃል እንደ ጣፋጭ መብል ነው።“ (መጽሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ ፲፷ ቁጥር ፰) ·       እፍታ ዛሬ ነው ከብራና ሳተናው የገባሁት። ትናንትና በተከታታይ የጻፍኳቸው የሰቆቃው አማራ ጉዳይ እና የእውነት ጠበቃ ማጣት በሚመለከት ስጽፍ ስለዋልኩኝ ጊዜ አልነበረኝም። ·        ወጣትነት እና መልካምነት ስለምን አይጣጣሙም? እኔ ወጣቶች ስለምን መልካም ነገርን ሊወርሱ እንደማይፈቅዱ ይጨንቀኛል። መልካም ነገር ዛሬ ላይ ካለወረሱ እንሱም ነገ መልካም ነገርን የሚፈራ ትውልድን ነው የሚተኩት። ቢያንስ ስለምን በመልካም ነገሮች ላይ ሚድያዎችም አትኩሮት ሊያደርጉ እንደማይፈልጉም አሁንም እኔ ይጨንቀኛል። የ66ቱ ዘመን እኮ እከሌ ተከሌ የለበትም። በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ከሴራ ጋር የተጋባ ነበር ንድፈ - ሃሳቡ። የጸዳ ተግባር ለመሸከም ሆነ ለመከወን ራሱ ንድፈ ሃሳቡ አይስችለውም። ለበጎ ነገር በሩ የተከረቸመ ነው። ለዚህም ነው ለዘመኑ ያልመጠኑ ቡቃያዎች ሳይበቅሉ በክፉዎች አረም ተውጠው ወይንም ደግሞ ከሰመው የቀሩት። ገና በለጋቸው ተባብሮ መቅበር ለምዶብናል።  እራስ እግሩ ማለት እስኪያስችል ድርስ ሸር ነው የሶሻሊዝም ንድፈ ሃሳብ። በመልካም ነገሮች ውስጥ የሚጠቀለለው የሸር መርዝ ነው። ሴራ ነው ድር እና ማጉ የሸማችን ዕጣ ፈንታ።  አሁን አንድ ሱዳን ላይ ያለ አጋርህ፤ ወንድምህ እንደ አንተ የተሰደደ ከልታማ ታማሚ ለህክምና የውጪ ዕድል ቢያገኝ ማሰናከል ከቶ ምን ይባል ይሆን? አንተ አትከፍልበት፤ አንተ ስፖንሰር አይደለህ።  ሌላ በጎ አድራጊ ደርጅት ሊከወነው ሲ