ልጥፎች

ከኦክቶበር 17, 2023 ልጥፎች በማሳየት ላይ
ምስል
  ዬኢትዮጵያ #የህልውና #መሠረታዊ #ችግር ጠሚር #አብይ #አህመድ ናቸው።     ምዕራፍ ፲፩ "አቤቱ የቤትህ ቅናት በላኝ።" እንዴት ናችሁ ክብረቶቼ? ደህና ሰነበታችሁልኝ? ፲ን የአብይዝም ለያዥ ለገራጅ ያስቸገረውን ዬ፭ ዓመታት ውጥንቅጥ የአገዛዝ ገፀ ባህሬ አስተውለን አሁን ወደ ፲፩ኛው ዛሬ እንሸጋገራለን። "ቂጥ ገሊቦ ራስ ተከናኒቦ" ስለሆነው የፋንታዚው ልዑል የጠሚ አብይ አህመድ ውቂ ደብልቂ እና ረግረግ። #በቅናት ፤ #በምቀኝነት ፤ #በማናንሼ #ድውይ ዕሳቤ ተነስተው ኢትዮጵያን እያመሷት የሚገኙት ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ ናቸው። ስለሆነም የኢትዮጵያ የህልውና ችግር ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ ናቸው። 1) የኢትዮጵያ፤ 2) የስሜን ኢትዮጵያ፤ 3) የአፍሪካ ቀንድ፤ 4) የመካከለኛው ምስራቅ አፍሪካ፤ 5) የአህጉራችን የአፍሪካ የችግር ምንጭ ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ እና ፈንታዚያቸው ብቻ ነው። ኢትዮጵያ በልዕልና ልቅና ዬነበራትን የተፈሪነት፤ የከበሬታ፤ የግርማ ሞገስ ማህባ ቦታ አውርደው የጣሉበትን ቦታ ውስጣችን እዬቆሰለ እዬታዘብን ነው። በሁሉም ዘርፍ ዛሬ ኢትዮጵያ ከደረጃ በታች ናት። ከትንሿ ከጁቡቲ እንኳን ጋር ስትነጣጠር። የሆነ ሆኖ የአህጉሩ አብሪ ኮከብ እሆናለሁ #አንጋጠው ልፍጭ ብለው ባይፍጨረጨሩ እንደ ተለመደው ባይሰሙም እንመክራለን። አይዘብዝቡ። አይዝረክረኩ። ሁሉን ነስቷቸው ሁሉን የሚፈልጉ መሪ መሆናቸው ደግሞ ይገርመኛል። ቅኑ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ! ከወፈፌ ጋር መወፈፍ ልማድህ አይደለም እና አደብህን ጠጥተህ፤ በተደሞ ተከውነህ ምክክርህን ከፈጣሪህ ከአላህ ጋር ብቻ አድርግ አደራ። እግዚአብሄር ደግ አምላክ ነውና ጨዋነትህን የሚመጥን ትጉህ፤ አዛኝ፤ አጽናኝ የአይዟችሁ ሙሴያዊ መሪ ይሰጥኃል። ጠብቀው

እናታዊነት በቅንነት ለውስጥነት።

ምስል
  እናታዊነት በቅንነት ለውስጥነት። • ለኩላሊት ድክመት ትንሽ ብልስ። „የሰው ልብ መንገድን ያዘጋጃል እግዚአብሐር ግን አካሄዱን ያቃናለታል።“ ጠብታ።             ባለፈው ሳምንት ስለ ኩላሊት ጠጠር ትንሽዬ አቅጣጫ ጠቁሜ ነበር። ምን ያህል እንዳዳመጣችሁት አላውቅም። ምን ያህል ሼር እንዳደረጋችሁት አላውቅም። ድውያኑ ማህበረ ግንቦታውያን ያው መኖራቸው ቀብር ስለሆነ ይህንንም ይገድቡት ያቅቡት ይሆናል። የሆነ ሆኖ መከታተላችሁን እያዬሁኝ ሚዛኑ ይለካል። በጣም የሚገርመኝ ሰው ሆኖ ተፈጥሮ ሰው መሆን የተሳነው ህዝብ ብዛቱ እጅግ ይገረምኛል። በቃ ልቡን አውልቆ፤ ህሊናውን አውልቆ እራሱን ተውሶ በውራጅ ማንነት የሚኖረው ህዝብ ብዛት ግርም ይለኛል። በራሱ የሚቆም የለም። እራሱን ሆኖ ተፈጥሮ ጨርቅ ቀዶ አልብሶ፤ መሃያ ከፍሎ ያላስተዳደረው ነፍስ እንዳሻው ይነዳዋል። ይገርመኛል። አቁም ሲል ያቆማል፤ ሂድ ሲል ይሄዳል። አድርግ ሲል ያደርጋል። አታድርግ ሲል አያደርግም። ሰው ራሱን ፈርቶ ከኖረ፤ ሰው እራሱን ወርጆ ከኖረ አልተፈጠረም ከምል አልተጸነሰም። ያልተጸነሰ ደግሞ ምንም ነው። {} • ኩላሊት ስለምን ይደክማል። • ሃኪም አይደለሁም። ሁለተኛ ደረጃ ተማሪ እያለሁኝ የባይወሎጂ እና የኬሚስተሪ ተማሪ ነኝ። አነባለሁኝም። እኔ እንደማስበው ግን የኩላሊት ድክመት ከሚያመጡ ውስጥ። (1) ኢንፌክሽን ወይንም ከዛ ጋር የተያያዙ በሽታወች ይመስሉኛል። በዚህ ዘርፍ ከቢቢሲ የ አማርኛው ክፍል እንዳነበብኩት ከሆነ ሽታ ያላቸውን ሳሙና ነክ ነገሮችን ለመታጠቢያ ነገር መጠቀም ለኢንፌክሽን እንደሚያጋልጥ አንብቢያለሁኝ። (2) ከዘር የሚተላላፍ ይህ ዕውነት የሆነ ነገር ነው። (3) የፉኛ ማነስ ይህም ዕውነት። አንዳንድ ኦርጋኖች ሲፈጠሩ አንሰው ይፈጠራሉ። ለምሳሌ ልብ። እና ፉኛ ትንሽ

መታቆር። oct 17.2020

  መታቆር። ህወሃት ሥልጣኑን ከለቀቀ ጀምሮ አቅም አባክኛ አላውቅም። ታግዬዋለሁ። ከሥልጣኑ ወርዷል። አሁን መታገል ያለብኝ ሰውን እዬገደለ ስለሰው አቀድኩ የሚለውን የኦዳ ሥርዕዎ መንግሥት ነው። ዛሬ ግን ባዬሁት የሁለትተኩል ዓመታት ትዝብቴ ግርም የሚለኝን ላነሳ ወደድኩኝ። ህሊናቸው ውስጥ የታቆረ ዕምቅ ድንብልብል መከራ አለና። የተነሱበት ፀረ አማራ፣ ፀረ ተዋህዶ ነው። በዚህ በለስ ቀንቷቸው 27 ዓመታትን ቢገዙም ግን ወድቀውበታል። አወዳደቃቸውም እርሾ አልባ ነው። አይመልስህ ተብሎ። የሚገረመው ነገር ከሚዲያ አዘጋጆቻቸው ከሊቅ እስከ ደቂቅ ዛሬም ህወሃት ሲመሰረት ከነበረው ዕሳቤያቸው አንዲት ስትዝር ፈቅ የለም። እርግማን። ሌላው ቀርቶ ምዕቱ 21 ኛው ክ/ ዘመን ሥልጣኔውም ዲጂታል መሆኑን የሉበትም። አንድም የህወሃት ፖለቲከኛ የወደቀበትን እንኩሮ ሃሳብ ኮንኖ ለመዳን ሲተጋ አይታይም። የሰው ልጅ የወደቀበትን መንገድ እንደምን መዳኛው አድርጎ ያመልከዋል? የተገለበጠ ጉድ። ያሉበት ቦታ የክብር ነውን? የሥነ - ልቦና ቀውስ የለባቸውምን? አማራ እኮ ነው ደግፎ ያስገባቸው፣ ያኖራቸውም የግርባው ብአዴን ሙሉ ድጋፍ ነው። የጣላቸውም የዚህን ድምፅ ማጣታቸው ነው። ማንም ይሁን ማንም የአማራ ድጋፍ ከሌለው ገዢ የመሆን ተስፋው ቅዥት ነው። አሁንም አገር ለመምራት ያስባሉ ህወሃቶች። ግን በፀረ አማራ ኃይሎች ስብስብ የበላይነት። አይሰቡት። አይዳክሩም። አይደለም እነሱ ኦህዴድ ቀፎውን ነው ያሉት። ኦህዴድም ፀረ አማራ ኃይሎችን ክበቡኝ ብሎ ሲመክር፣ ሲዘክር ባጄ፣ የምድር እንቧዩን ብአዴንን በሞጋሳ ጥምቀት አስምጦ እንደ ደመቅን እንቀጥላለን ብሎም አሰበ። 50/60 ወጥቷል ትልሙ። አይደለም ለዛን ጊዜ አሁንም ያለው በቀውሱ የኦፕሬሽን ትንፋሽ ነው። በፋቲክ። ህወሃት ከራሱም ውድቀት

ናርጋ ስላሴ ቤተክርስቲያን !

ምስል
ናርጋ ስላሴ ቤተክርስቲያን ! ናርጋ ስላሴ በጣና ሐይቅ አማካኝ ርቀት ላይ በሚገኝ ትልቁ ደሴት 'ደቅ' ደቡባዊ ጠርዝ ላይ የሚገኝ ነው፡፡ ይህን አብያተክርስቲያን ያሰሩት በጎንደር ዘመን ከነበሩት ትልቅ ሰው መካከል እቴጌ ምንትዋብ ናቸው፡፡ ናርጋ እቴጌዋን ጨምሮ ከበርካታ ነገስታትና የዕምነቱ አባቶች የተበረከቱ ፎቶው የሚተየውን ጨምሮ ንዋዮ ቅድሳት ይገኙበታል፡፡ ደቅ ደሴት ከጣና ደሴቶች ትልቁ ሲሆን በወስጡ 7 ያህል አብያተክርስቲያናትን የያዘ ነው፡፡ ከደሴቱ ምስራቅ ዳርቻ የጎንደር ነገስታት አስከሬን በክብር ያረፈበት ዳጋ እስጢፋኖስ ገዳም ይገኛል፡፡ ናርጋ ስላሴ ከጣና ሐይቅ ደሴቶች በስፋቱ አንደኛ ከሆነው ደቅ ደሴት ላይ በምዕራባዊ ክፍሉ የሚገኝ ቤ/ክርስቲያን ነው።  

የአብይዝም ሸምቀቆ። oct 17.2019

የአብይዝም ሸምቀቆ። የአብይዝም ሸምቀቆ ከድንገቴው ሱናሜ ጋር ቀለበተኛ ነው። አሁን አንድ ህብረ ብሄር ሚኒሻ ማደራጀት ፈለገ። ሌት እና ቀን ጦር ማደራጀቱ እንዳይነቃበትም ዘያ።ዬደ። ቅምጡን አስነሳ እና አስፎከረ። ብቅ ብሎ ዲስኩር አደረገ። ዲስኩሩ በእንግሊዘኛም ተቀኝቷል። ለጀርባ አጥንቱ ለአቶ ኽርማን ኩኽን ነው ነገርዬው። ፋከራው አማራን እናስታጥቃለን። እቅዱ የአማራ ታጣቂ የሚባል የለም በጥላቻ የመገለውን መንፈስ አሰባስበን የራሳችን ጉዳይ እናስፈፅምበታለን ነው። እራሳቸው ጠቅላዩ አማራ የሚል ቃልም ህዝብም መስማት አይሹም። የሰይጣን ጆሮ ይደፈን እና በአንድ ቀን ምጥጥ ብለን ብናድርላቸው ይሻሉ። አይወዱንም። ተዋህዶም የባዕለ ዕለቷን ከሚሰሙ ቢሞቱ ይመርጣሉ። ከራሳቸው ጋር እርቀሰላም ሳያወርዱ ነው አስታራቂ የሆኑት። ለዚህ ደግሞ ታጥቀው ተነስተው በሁሉም ዘርፍ ምንጠራውንም፣ ስረዛውትም ሁሉንም ዓይነት መከራ በጥድፊያ እያጣደፋት ነው። የልግጫው ልግጫ በዛ ሰሞን ሙሉ አቅም አለኝ ያለ መከላከያ ዛሬ የቤንሻንጉልን ሸፍጥ ከአቅሜ በላይ ነው ይላል። አሁንም የሰይጣን ጆሮ ይደፈንና የውጭ ኃይል ቢወር ምን ሊኮን ነው። ለአንድ ጭንጋፍ የጫካ ሽፍታ ሌላ ሚሊሻ የሚደራጅለት? የግብፅ ሠራዊት ነውን? ለነገሩ ቀውሱ እንዲቀጥል ይፈለጋል። ያው ለዛ መተተኛ ምርጫ ሲባል አማራም ኦርቶዶክስም ይገበራሉ ለ10 ዓመት። ሁለት ተርም ነው ዕቅዱ። ሞት ንክች አያደርገውም ቤተ መንግሥቱን። ሌላም መፈንቅል አያሰጋውም። ደኃ የአማራ ገበሬ ግን ስጋቱ ነው። ለምን? ቁጥሩ፣ ክህሎቱ፣ የመቻል ጥበቡ፣ ጨዋነቱ፣ የሥነ - ልቦናው ልቅና ቦንብ ነው በበታችነት ለሚማስነው ዝክንትል ህሊና፣ ድሪቶ ልብ ሁሉ። እና ጠቅላዩ ብቅ ብለው የሸመቁትን ሸምቀቆ በሌላ በርዥን ይዘው ብቅ ብለዋል። ከሁሉ በላይ ግን ፈ

እቴጌ መቀሌ 0k17.2019

ህም። ነው ዘንድሮ። እቴጌ መቀሌ ጦርነት አውጃ፣ ጁቡቲን ሱማሌ ላንድ ሌላ ጥቃት ሰንዝረው፣ ጎንደር ከተማ ዙሪያውን ቀውጢ ሆኖ፣ ድሬ እና ሀረር ጎረምሶች እዬመሯት፣ አጣዬ እና ኬሚሴ ሌላ ጦር ታውጆ፣ አዲስ አበባ በጭንቀት ተወጥራ፣ አዳማ፣ ደብረዘይት በጎረምሳ እዬታመሱ፣ የውህድ ፓርቲ ዘፈን ይደለቃል። መሬት እኮ ልትፈነዳ ተቃርባለች። እራሱ መከላከያ በዬዞጉ ጎድቯል ወይንስ ልቡ ከኖቤል ተሰክቶ ይሆን? ይህም አይታወቅም። ይህም አይደመጥም። ይህ ሁሉ ታምቆ ቤተ መንግሥት አንድ ጊዜ ከካቢኔው ሌላ ጊዜ ከኦዳ ዛፍ ጋር ፈንጠዝያ ላይ ነው። የዲፕሎማት ማህበረሰብም አንድ ነገር ቢፈጠር መውጫችን ብለው ያሰቡት ነገር የለም። ሌላም መገዳደል ይኖር እላለሁኝ የኦዳውን ዛፍ አስተውዬ በአርምሞ እያዬሁ። ይጨንቃል። ያስፈራል። ፀሎት።

ኦዳ እና አዲሱ የኦነግ ኦዴፓ የኃይል አሰላለፍ። 2019

ኦዳ እና አዲሱ የኦነግ ኦዴፓ የኃይል አሰላለፍ። ኦዳን ይሳለሙ ዘንድ ጠሚር አብይ አህመድ ቲም ጃዋርን የካደው የኦነግ ኦዴፓ የለሜ ቲም ምህረት ጠይቋል። ኦዳ ለአማላጅነት ቀርቧል። የራበው ልጅ ጡት ሲያጎርሱት እንደሚፍለቀለው በልጃዊ ባህሪ የሚታወቁት ጠቅሚር አብይ አህመድ ኦዳን ትኩር ብለው እያዩ ተፍለቅልቀዋል። ሌሎችም ክልሎች ድርጅታዊ ሥራ ተስጥቶ ይህን ይከውናሉ ብዬ አስባለሁ። ትግራይን አይጨምርም። የሚገርመው በጠቅሚሩ የሥልጣን ሹመት አፍንጫኽን ያሉት የኦሮምያ ከተሞች በፌስታል ፖለቲካ አራማጁ በአቶ አዲሱ አረጋ አሰተባባሪነት የኖቤል የድጋፍ ሰልፍ እጣ ነፍሳቸውን ወጥተዋል። ይህ የፖለቲካ ቁማር ትልቅ ፍሬ ነገር ይነግረናል። ከአምስት ተተርትሮ የነበረው ኦዴፓ ወደ አንድ ማጋደሉን። ኦዴፓ ውስጥ፣ የጃልማሮዊ፣ በቀላውያን፣ ጃዋርውያን፣ ለማውያን፣ አብያውያን፣ ዳውዳውያን ነበሩ። ግባቸው ኦሮሞን የአፍሪካ ገዢ አድርጎ ማውጣት ቢሆንም የቴክኒክ ጉዟቸው ግን ዥንጉርጉር ነበር። ይህም በመሆኑ ኦሮምያ ከፌድራሉ አፈንግጦ በራሱ ጊዜ ሉዕላዊ መንግሥት ሆኖ ቆይቷል። ኢትዮጵያም በዚህ የታበዬ መንፈስ ስትቀጠቀጥ ለ15 ወራት ባጅታለች። ኦነጋውያኑ፣ የኦሮሞ ሊሂቃን የጠሏት ኢትዮጵያ የኖቤል ተሸላሚ አድርጋለች። ለዚህም ነው ሥርጉትሻ ለረጅም ጊዜ የዘለቀ አስተምህሮ የነበራት። ኢትዮጵያዊነት ከመፈጠሩ በፊት ፈተናን አሸንፎ የተፈጠረ ሚስጥር ነው በማለት ኢትዮጵያን ስትዘክር የኖረችው። የሆነ ሆኖ እጅ የሰጠው የለማ ኦዴፓ ቡድን የጃዋር ቡድን ከድቶ ኦዳን በወርቅ አሰርቶ ምህረት ጥዬቃ ላይ መሆኑን አይተናል። የሚገርመው የኦነግ ኦዴፓ ቲም ለማ ጃዋርን መክዳቱን በፕሮፖጋንዳ ግርዶሽ ለመከለል መሞከሩ ኢትዮጵያ ማስተዋል ያላቸው ልጆች የሏትም የማለት ቧልት ነው ለእኔ። የጃዋር ቲም ለለማ ቲ

የጃዋራዊው መንገድ 2019

  ይህን መረጃ ከልቤ ሆኜ መፈተሽ ፈልግሁኝ። ሦስት ሰዎች ለእጩ ምከ ከንቲባነት እንደቀረቡ። ሁሎቹም ኦነግ/ኦዴፓ ናቸው። ነገር ግን የኃይል አሰላለፋ ከኖቤል በፊት እና በኋላ ተብሎ መታዬት ይኖርበታል ባይ ነኝ። ከኖቤል ሽልማት በፊት ቲም ለማ፣ ቲም ጃዋር፣ ቲም አብይ ነበሩ። ቲም አብይ አማራን በመጫን ብቻ ያተኮረ ተግባር ነበረው። ብዙም በወጣበት ድርጅት ሚና ያልነበረው፣ ተፅዕኖ ማሳረፍ የማይችል። ሌላው ቲም ለማ ኦሮምያን ማዕከል አድርጎ በኢትዮጵያ ፖለቲካ የኦሮሞን የበላይነት ማስጠበቅ ላይ መሠረት ያለው ተግባር ሲከውን የቆዬ ጉልበታም መንፈስ የነበረው ነበር፣ ቲም ጃዋር ደግሞ ለኦሮሞ ፖለቲካ ልዕልና የሌሎቹን ሰላም በማወክ ለቲም ለማ አቅም ለፌድራል መንግሥቱ ምጥ ሲጥድ የባጀ ነው። በሌላ በኩል በጠሚር አብይ ሹመት ማግሥት ከቢቢኤን ጋር በነበረው ቆይታ የዶር አብይ ሰብዕና ስላቁን ለማሳካት ጅዋጅዊት እያጫወተ አይሆኑ አድርጎ ሰብዕናቸውን ውልቅልቁን አውጥቶታል። ቀድመን የሞገትንላቸው ሰዎች በልፍስፍሱ አቅማቸው ከውስጣችን ፍቀናቸዋል። ይህን የጃዋራዊው መንገድ አንድም ቀን አቶ ለማ መገርሳ ሲኮንኑት ተደምጠው አያውቁም። ሁሎቹም የሚመሳሰሉበት በፀረ አማራ ፍልስፍናቸው እና የኦሮሞን ተጠቃሚነት በሚመለከት ብቻ ነው። የኢትዮጵያ መዋለ መንፈስ እንዲውል የሚፈለገውም ለጋራ ግባቸው ኢትዮጵያን ኦሮማይዝድ በማድረግ ተልዕኮ ነው። አሁን ቲም ለማ ቲም አብይን ይቅርታ የጠዬቀበት ሁኔታ እዬታዬ ነው። የትናንቱ የኦዳ ዛፍ ሃብል እና የጥቅምት ሁለቱ የድጋፍ ሰልፍ የምህረት ጥዬቃ ብቻ ሳይሆን የኃይል አሰላለፋ መቀዬሩን ይነግረናል። ለዚህ ነው ዛሬ ቲም ለማ እና ቲም አብይ አብረው እንደ ነበሩ እዬተተረከልን ያለው። የቲም ለማ ሰብዕና አዲስ ግንባታ እዬተደመጠ