ልጥፎች

ከጁን 19, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ዕንቁ ሴኒጋል 2 ለ 1 አሸፈ።

ምስል
የአርንጓዴ ቢጫ ቀይ ዕንቁ ሲኒጋል አውሮፓዊውን የፖላንድ ቡድን  ሁለት ለአንድ አሸነፈ። ከሥርጉተ ሥላሴ 19.06.2018 ከሲዊዘርላንድ። "በጎ ነገር ከጥንት ጀምሮ ለበጎ ሰዎች ተፈጠረች፤ እንደዚሁ ክፉ ነገርም ለሃጢያተኞች ተፈጠረ" (መጽሐፈ ሲራክ ምዕራፍ ፴፱ ቁጥር ፳፬) እቴ ድንቡልቡሊት ሉላዊ አቅመኛ ሁሉ ያገኘ ባሰኘው መንገድ ይደልቀኝ ብላ ራሺያ ከተመች። አቤት እንደ እሷ ፍቅርን በመደለቅ የሚያሽሞነሙን እኮ የለም። ውበቴ ነው ድለቃ ትለላች። ድለቃው ላብ በላይ ሲያደርገኝ አራጋቢዎቼ አሉልኝ። እልልታው ሲያመረኝ ደግሞ ሌጋባው ፊሻካ የት ሄዶ ትለናለች። ብቻ የዘንድሮ የዓለም ዋንጫ ርስት ተደረገ፤ ዕድሜ ለመደመር ፖለቲካ … በሉ ዛሬ አንድ ጨዋታ አዬሁኝ። ሙሉውን።    ስችል ቀን ስመለከት አልጨርሰውም አገራዊ ጉዳይ አዳዲስ ክስተቶች ስላሉ ሙሉውን አልከታተለውም። የሆነ ሆኖ ካዬሁት ብዙም ድንቅ ጨዋታ አልገጠመኝም። አንዳንድ ጊዜ ታጣፊ አልጋ የገዙ እስኪመሰል ድርስ አሰልቺም ነው። ዛሬ በሲዊዙ ሰዓት አቆጣጠር 17.00 ሰዓት ላይ የተጀመረው ጨዋታ ሁለት ለአንድ በሆነ ውጤት ተጠናቀቀ። ጨዋታው አፍሪካዊዉ የሴኔጋል ቡድን ከአውሮፓዊው ከፖላንዱ ጋር ነበር። እውነት ለመናገር እስከ አሁን ከዬኋዋቸው ጨዋታዎች በጣም በተሻለ ሁኔታ ነበር። በተለይ በመጀመሪያው የጨዋታ ክ/ ጊዜ የሴኔጋል ቡድን ጥበባዊ ጨዋታ ማራኪ ነበር። አንድ ጎል አስቆትሮ ነው ለ እረፍት የወጣው። በጠቅላላ በጨዋታው ይዘትም ፖላንድ በመከላከል ሴኔጋል በማጥቃት ሲጫወቱ ከቆዩ በኋዋላ በመጨረሻ ደቂቃ ላይ ፖላንዶች ድንቅ የሆነች ግብ አስቆጠሩ እና እና አንድ ለሁለት ሆኖ።  በቀሩት ባለቁ ጥቂት ቅርጥምጣሚ ደቂቃዎች ፖ

የፍቅር ትርፉ።

ምስል
የፍቅር ትርፉ ፍቅርን ለፈቀዱ ብቻ ይገለጥላቸዋል ! ከሥርጉተ ሥላሴ 19.06.2018 (ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ) "እግዚአብሄር እርሱን መርጦታል እና።  ለባለ መድኃኒት ሥራውን                ሥራለት እሱን  ትሸዋለህና ካንተ አታርቀው"            (መጽሐፈ ሲራክ ምዕራፍ  ፴፰ ቁጥር ፲፪) የፍቅር ተፈጥሮ መርህ ትርፍ ኪሳራ የለሌበት ብቻ አይደለም። በኪሳራ ውስጥም ትርፍ አለ። ለምሳሌ አንድ ሰው ለሌላው ሰው በሚሰጠው ፍቅር ውስጥ እሱ ይቅርብኝ የሚለው ነገር ይኖራል። ፍቅር በመስጠትና በመቀበል ውስጥ የተፈጠረ ሲሆን በመስጠት ውስጥ ሰጪው የሚያጣው ወይንም የሚጎድልበት ነገር ሊኖር ይቻላል። የሚጎድለው ነገር ምንአልባትም የኑሮው አንኳር ጉዳይ ሊሆን ይችላል። ነገር ግን ፍቅርን ፈላጊ ከሆነ ያን አንኳር የህይወቱን ጉዳይ ቅርብኝ ብሎ ፈቅዶ የፍቅሮን ስጦታ በተግባር ሊያከብረው ይችላል።   ፍቅሩ የከበረ ሊሆን የሚችለው ግን ፍቅርን ተቀባዩ የተወዎ አንኳር ጉዳይ ቢኖር እንኳን   ሊጸጸተው ወይንም በምልሰት ሊያውከው እንዳይችል አድርጎ ከወሰነበት ብቻ ነው። እርግጥ ፍቅር ከተተወው ጉዳይ በላይ እንዲያውም በላቀ መልኩ ረቂቅም ሊሆን ይቻለል። መንፈሳዊ ትርፉ አጥጋቢ ነው። ሰው ለሚወደው ነገር እራሱን ሲገብር ለወደደው ነገር ፍቅር ስለሰጠ ነው። ያ የወደደው ነገር ላይመቸውም ይችላል ግን በወደደው ነገር ውስጥ መኖርን መፍቀድ በራሱ ፍቅርን በመስጠት ብቻ ምላሽ ሳይገኝ ደስታን ማግኘት ይቻ

መኖር እንዲያምርበት።

ምስል
መኖር እንዲያምርበት …           ከሥርጉተ ሥላሴ …. 09.02.204 ( ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ)               "ጥበብ በቀደሙ ሰዎች ሁሉ ዘንድ ተመረመረች።" (መጽሐፈ ሲራክ ምዕራፍ ፴፱ ቁጥር ፩) አዳም እንደተቆለፈ ነውን? …. ከአህዱ በፊት በዚህ ጉዳይ ዙሪያ እንድል ፈቀደ አባቴ ….. እሱ እራሱ ለሰጠው ሥጦታ ጊዜን ተመኙ ባለሙሉ ባለሥልጣኑ ክርስቶስ ነውና። ጥበብ እራሱን ፈልጎ ያገኛል። በጮሪት ወይ ቀን - እኩል ላይ ወይንም ከብት ግባት ወይ በግርማ ሞገስ ታጅቦ ድንግዝግዝን ተገን አድርጎ እረፍት በሚሰጠው ….. በተጨማሪነት ወይንም በማሟያነት አልነበረም፤ በክፍት ቦታ ሸፋኝነትም አልነበረም፤ እንዲያምርብን - እንድንዋብ - ሰውነታችን ኃይል ኖሮት የኑሮን ዝክንትል ሳይቀር ደስ ብሎን እንሸከም ዘንድ፤ የተቆጣጠሩ ችግሮችንም ለመዳኘት ነው የተፈጠረቸው - ሴት። ስለ ድርጅት መፈጠር ስናስብ እስትንፋሳዊ የድርጅት ሰቅ አድርጎ የፈጠራት ሴትን ነው አባታችን። የመጀመሪያው የህይወት ባለሙሉ ሥልጣን የመፈቃቀድ ድርጅተ ጥንስስ ሚስጢር ናት ሴት። ህይዋን ባትፈጠር ዓለም ወላቃ ትሆን ነበር። ዓለም ያዳልጣት ነበር። ትውልደ - አዳም ላይ ያቆም ነበር። ፋዳሳዋ አላም በአንድ እግሯ እንደቆመች ቆሞ ቀር በሆነች ነበር። ወጣ ገቧ ዓለም ቀን ተሌት የማይለይባት ገድል በሆነችም ነበር - አጥንት ነገር። የጡት - እትብትነቱ መገለጫውም ሴት የእናቷን መክሊት ፈጻሚ አድርጎ ትውልድን