#በቁሙ #ቀብር #ላይ #የዋለ #ብትክትክ እንኮሸሽሌ #ዕሳቤ።
#በቁሙ #ቀብር #ላይ #የዋለ #ብትክትክ እንኮሸሽሌ #ዕሳቤ ። "የቤትህ ቅናት በላኝ።" Anchor Media ''ጦርነቱ ቢጀመር ደስ ይለኝ ነበር። ...ከዚያን በኋላ የኢትዮጵያ ህዝብ እፎይታን ያገኛል'' ፕ/ር መሀመድ ሀሰን» https://www.youtube.com/watch?v=XotdIljSVEA ይህቺ አገር ኢትዮጵያ ስንቱን ዝክንትል ዕሳቤ፤ ስንቱን ድሪቶ ምልከታ፤ ስንቱን ስቃይ #ጠሪ ዕሳቤ እንደ ተሸከመች አመላካች ነው። እርእሱን በቁሙ ያለ ተርጓሚ ስታነቡት። ጥገኝነትን ተጠይፋችሁ አመሳጥሩት። የጦርነት ናፍቆት ለእኔ ጭካኔ ነው። በዚህ ጭካኔ ውስጥ ኢትዮጵያዊነትን እስቲ አፈላልጉ? ግን ማህበረ ቅንነት እንዴት ናችሁ? ከሠራተኛ መሪነት፤ ከሊቃውንትም፤ ከዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ሥመጥሩነት፤ ከቀደምት የነፃነት ታጋይነት፤ ከመሪነትም ጎራ የሚመደቡት ባለሁለገብ የልምድ ባለቤቱ ፕሮፌሰር መሐመድ ሃሰን በጦርነት " #እፎይታ " ይገኛል ይሉናል። ማን በሚመራው ጦርነት ብላችሁ ጠይቁልኝ በትህትናም። ሎቱ ስብኃት። ለእኔ ዝርግ ዕሳቤ ነው። ለእኔ ይህ አንካሳ ዕሳቤ ነው። ፍላጎቱ በግራ ቀኝ ቢኖር እንኳን ይህን ኩፍኝ መንገድ ማበረታት፤ ከጃርታዊው ጦርነትም ተስፋን መጠበቅ እርቃኑን የቆመ ምኞት ነው። እርግጥ ነው አጃቢ ይኖረዋል። ለእሳት ማገዶ እንደሚቀርበው። ግን ለትውልድ ፀር የሆነ አጥፊ ዕሳቤ ነው። ፕሮፌሰር አንድ ጊዜ አንከር ሚዲያ ላይ "ኢትዮጵያ የሚለው ሥያሜ #ባይስማማን ልንቀይረው ተነጋግረን እንችላለን" ሲሉ #እግዚኦ ብዬ ነበር። ጋዜጠኛ አቶ መሳይ መኮነንም እናቱ ማንነቷን ሊገፍ የሚችል እጮኛ ግን ድውይ ሃሳብ ሲፈልቅ አልሞገተም። ዝም ብሎ አሳለፋቸው። እ...