ልጥፎች

ከማርች 27, 2025 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ስለምን ይሆን የኢትዮጵያ ፖለቲካ #አጽናኝነትን እንደ ጦር የሚፈራው?

ምስል
 ስለምን ይሆን የኢትዮጵያ ፖለቲካ #አጽናኝነትን እንደ ጦር የሚፈራው?  ለምንስ ይሆን #አይዟችሁ #ባይነት እንደ ወንጀል የሚታዬው?  በኢትዮጵያ ፖለቲካ #ሰዋዊነት #አደጋ ውስጥ ነው።  ይህ አካሄድ ጨካኞች፦ በጭካኔያቸው ጀግንነት እንዲሰማቸው የሚያደርግ ነው።  የኢትዮጵያ ፖለቲካም ለጨካኞች ሽፋን ስለሰጠ የፖለቲካው አውራ መሪ እኔ ነኝ፤ ሥራም ሠርቻለሁ ይላል።  ፖለቲካ ሠሪው #ሰው ነው። ፖለቲካ የሚሠራውም #ለሰው እና #ለተፈጥሮ ነው።  ስለሆነም #ሰውኛነት ቢያስመሰግን፤ ቢያስከብር እንጂ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ህግ #መሳደጂያ ሊሆን አይገባም።  የኢትዮጵያ ፖለቲካ ከሰውኛ ማዕቀፍ ውስጥ #ያፈነገጠ ነው።  ይህን ማረቅ እና ማሰተካከል ይገባል። #ሃግ ሊባል ይገባል። የኢትዮጵያ ህዝብ በተፈጥሮው አዛኝ፤ ሩህሩህ፤ ደግ እና አጽናኝ ነው።  ሃዘኑን በወል በህብራዊነት አስከብሮ የኖረ ህዝብ ነው።  ይህን #ጸጋውን #የሚገፍ #አሳቻ ዘመን ላይ ነውና በጥሞና የኢትዮጵያ ህዝብ ሊያስብበት ይገባል። ገዢወቹንም ሊያርማቸው፤ ሊገስፃቸው፤ ሊቆጣቸው ይገባል።  ሥርጉትሻ2025/03/26

አገር እናት ናት። እናትም አገር ናት። እናት እና አገር #ትርታ ናቸው ለመኖር።

ምስል
    አገር እናት ናት። እናትም አገር ናት። እናት እና አገር #ትርታ ናቸው ለመኖር።  መኖርም ሆነ አገር እናትነትን #ያከበሩ ሊሆን ይገባል።  እናትነት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ከክብሩ በታች እዬታዬ ነው። ትናንትም ዛሬም። ሁልጊዜ መገበር።  እናትነት የዓለም ገዢ #ምህዋር ነው። እናትነት ድንቅ እና ውድ ፀጋ ነው።  እናትነት አስማሚ፤ አረጋጊ፤ አጽናኝ እና ኃላፊነትነትን እና ተጠያቂነትን በተፈጥሮው ልክ ገቢር ላይ የሚያውል #ምሩቅ በረከት ነው።   #እናትነት #የፈጣሪ #የመመረቅ #መግለጫ ነው ማለት እችላለሁኝ።  እናትነት የፈጣሪ እና የተፈጥሮ የሚስጢር #ምስባክ ነው። እናትነት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ግን #ሰቀቀን ውስጥ ነው የኖረው።  እናትነት በኢትዮጵያ ፖለቲካ የሃዘን ድንኳን ውስጥ መኖሩ #እንዲከትም የተገደደ ክስተት ነው።  እናትነትን ሳያከብሩ መቅረት የአገርን #ምርቃት ከጉልላቱ ያስነሳል። የፈጣሪ ቁጣን መካችም የለም ከመጣ አፋጣኝ እርማት ሊወሰድ ይገባል። እናትነትን የኢትዮጵያ ፖለቲካ በእጅጉ እዬተዳፈረው ነው።  የኢትዮጵያ እናቶች #ጡታቸውን አሽተው ቆርጠው ከረገሙ ወዮልሽ ኢትዮጵያ ነው። ይህን በጣም ነው እኔ እምፈራው።  እናትነት በኢትዮጵያ ጭቆና ውስጥ ነው። ግፍ እዬተፈጸመበት ነው። የእናቶች ንቅናቄ ከተነሳም አደጋው ዘርፈ ብዙ ነው። ብልጽግና እናትነትን ከጥንስሱ ጀምሮ ፈተና ውስጥ ጥዶታል። ተንገርግቧል - እናትነት።