ልጥፎች

ከፌብሩዋሪ 8, 2025 ልጥፎች በማሳየት ላይ

#የአንከር ሚዲያ ሰሞናተ - ሙግቱ ይበል ያሰኛል። ሚዛን ግን ይጠይቃል ሰላሙ ለአማራ እናትስ ይላል።

ምስል
  #የአንከር ሚዲያ ሰሞናተ - ሙግቱ ይበል ያሰኛል። ሚዛን ግን ይጠይቃል ሰላሙ ለአማራ እናትስ ይላል።   "የቤትህ ቅናት በላኝ።"       ትናንት ጋዜጠኛ መሳይ መኮነን ከአቶ ሚኪ ተስፋዬ ጋር ቃለምልልስ ነበረው። ሙሁራን አቅርቦ ሲሟገት እከታተለዋለሁኝ። ተደማጭም ጋዜጠኛ ነው። እንግዶቹን ወደ እሱ ምልከታ ለማምጣት የሚያደርገው ፍልሚያም የጉድ ነው። ድሮ ድሮ በብዙ እሞግተው ነበር። አሁን ሙግት አቆሚያለሁኝ። እሚገርመኝን አመክንዮ ግን ማቅረብ ግድ ይሆናል። ከተደመጠ #ስርክርክ የሚሉ ዕሳቤወችን ማጽዳት ይገባል። ጋዜጠኛ መሳይ መኮነን የትግል ሚዲያ ክፍሉ ይመስለኛል። ዝንባሌውም ወደዛ ነው። የሆነ ሆኖ ሰሞኑን ግን እሱን እራሱ በራሱ ሚዲያ የሚሞግቱት በርክተዋል። በተራው እዬተሞገተ ነው። ይህ ሸጋ ገጠመኝ ነው። የጠበቃ አርበኛ አስረስን ሙግትም አዳምጫለሁኝ።   ጠበቃው ቀላል አልነበረም። ፍላጎቱን አስከብሮ ነበር ውይይቱ የተጠናቀቀው - በእኔ ሚዛን አርበኛ አስረሱ አሸንፏል ባይ ነኝ።።። ብቁ ወጣት ነው ጠበቃ አስረስ። ለህይወቱ ግን #እሳሳለታለሁኝ ። አይደለም ለአማራ ለኢትዮጵያም የሚጠቅም፦ እራሱን በአግባቡ መግለጽ የሚችል ወጣት ነው። በሚያምንበት ሃሳብ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ማሳ ቀለመ #ህብር ያደርገዋል እና። ሰላሙ ቢገኝ።   ትናንትም አቶ ሚኪ ተስፋዬም እንደ ጉድ ነበር የሞገቱት ጋዜጠኛ መሳይ መኮነንን። ኢትዮጵያ ውስጥ በዜግነት ፖለቲካ ላይ የሚሠራ #ሰላማዊ ታጋይ ይህን ያህል አቅም ያለው አለን ብያለሁኝ። ሚዛን ላይ ሆነው የሚያምኑበትን ፋክት አላስነካም ብለው በድፍረት፤ በእርግጠኝነት ወሳኝ በሆኑ አመክንዮወች ጋዜጠኛው እስኪበቃው ተሞግቷል። አልተበገሩለትም። ደስ የሚል ፍልሚያ ነበር። ...

#አንዱ #የእኛ #ግርማ - የዘመን ሁነኛ! የሚሊዮኖች ድምጽ ይጮኃል!

ምስል
  የሚሊዮኖች ድምጽ ይጮኃል! አዳኝን ገድሎ የውስጥ ሰላም ይሰደዳል። ለገዳዮች በከንቱ የፈሰሰው የፈው የደም ጠብታ ሁልጊዜም ይጮኃል! እዮራዊ ርትህ ይሻልና!   "የቤትህ ቅናት በላኝ።"                 #አንዱ #የእኛ #ግርማ - የዘመን ሁነኛ!   ዕንባ~~~~ ባባ በዕንባ~~~~ ዘንባባ ስለራሱ~~~ አነባ። በባሩድ~~~ ድብደባ በጭካኔ~~~ ደባ ዕንባ~~~ ባባ ስለራሱ አነባ። የሰውነት~~~~ ዓርማ ነበር~~~ ለእማማ #አንዱ የእኛ ግርማ የዘመን ሁነኛ! ቡቃያ~~~ ሲነቀል~~~ሲነቀል ዋይታ~~~ ሲበቃቀል~~~ እህህህ~~~ #ህህ ሲተከል --- ሲተከል፦ ንፁኃኑ በግፍ እንዲህም ሲገድል ዕንባ ይኽው ባባ ስለራሱ - አነባ። የበቀሉ ብቅል #ከ -አረሙ ከርፍቷል ትውልድ በምንጣሮ መጠጊያ ተነጥቋል። ዘረፋ - ዘረፋ -- የትንታግ ዘረፋ~~~~ የእስትንፋስ ዘረፋ~~~ የመኖር ዘረፋ --- ዘረፋ~~~~ዘረፋ የዕድሜ ---- ዘረፋ --- የትውልድ ዘረፋ ~~~ #የዊዝደም ዘረፋ #ከረፋ ! 06/02/2025 12.00 ሰዓት። ቢንተርቱር። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 08/02/2025

#የአማራን #እናትን #ማሳደድ #ይቁም!

ምስል
  #የአማራን #እናት #ማሳደድ #ይቁም ! #አማራን #የሚከብሩ #እኛወችን #ማንገላታት #መግፋት ፦ #ይቁም ! #ቋያ #ውስጥ #ስቃይ ላይ የሚገኙት የአማራ ህዝብ #የዘመናት ስልጣኔ #ትንታጎች ! ኑሩልን። አሜን።                ሥርጉትሻ2025/02/08 አማራነት ይከበር! ፍትህ ለአማራነት! የአማራን እናት #ማሳደድ ይቁም!