ልጥፎች

ከዲሴምበር 18, 2023 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ከማን የተማሩትን፨ የኦሮሞ ፖለቲካን ጎለጎታ እየላኩት ነው፨ "#ሸለፈታም።" የኢትዮጵያ ጦር ኃይሎች አዛዥ ጠቅላይ ሚር #አብይ #አህመድ። "#ማበሳበስ። ስድ አደግ" ጄኒራል #ብርኃኑ #ጁላ የኢትዮጵያ ጦር ኃይሎች ኢታማጆር ሹም። ሁለት ቁንጮወች ወደ ጅራትነት አሰኛቸው።

ምስል
  ከማን የተማሩትን፨ የኦሮሞ ፖለቲካን ጎለጎታ እየላኩት ነው፨ " #ሸለፈታም ።" የኢትዮጵያ ጦር ኃይሎች አዛዥ ጠቅላይ ሚር #አብይ #አህመድ ። " #ማበሳበስ ። ስድ አደግ" ጄኒራል #ብርኃኑ #ጁላ የኢትዮጵያ ጦር ኃይሎች ኢታማጆር ሹም። ሁለት ቁንጮወች ወደ ጅራትነት አሰኛቸው።   "ከንቱ የከንቱ ከንቱ ሁሉም ነገር ከንቱ።"     # በር እኔን ስለመግለጽ።   ፊልዴም አይደለም። የማይመለከተኝን ዘርፍ አልነካካውም። መከላከያን በሚመለከት ዝምታዬ ከመቃብር የሚከብደውም ለዛ ነው። ኢኮኖሚ ዘርፍንም ትውር እማልልበትም በዚህው ሎጅክ ነው። ሁሉም ዘርፍ ባለሙያ፤ ኤክስፐርት ፈላስፋም አለውና። #የማህበረ ኦነግ ካሪክለም ጠያፍ ቃላትን መዳፈር።   የማህበረ ኦነግ የአይዲኦሎጂ ካሪክለም ግን ይገርመኛል። ማህበረ ኦነግ በፖለቲካው ዘርፍ በብሄራዊ፤ በአህጉራችን በእማማ አፍሪካ፤ በምዕራብውያን እና በአውሮፓውያኑ እንደዚህ ዘመንም ከፎቅ የተፈጠፈጠበት ዘመን ያለ አይመስለኝም። በታሪኩ ኦነግ የኢትዮጵያን ማዕከላዊ መንግሥት #አራጦ እንዲመራ፤ በትረ ሥልጣኑም ያለ ከልካይ ተሰጥቶት በወርደ ጠባቡ ቁመናው ኢትዮጵያን መምራት ተስኖት በዚህ መልክ ወድቆ ማዬት ጊዜ ራዲዮሎጂነቱን አስመስክሯል።   ዛሬ ስለ አጤ ጊዜ ቅኔነትም ልከልለት። አወን! ጊዜ #ቅኔም ነው። አጤ ቅኔ ቅኔውን በተሰጠው ልክ እንዲህም ይዘርፈዋል። ለቅኔ ማህበረ ኦነግ ስለማይችሉት ሲዋጉት // ሲወጉትም በበታችነት ስሜት ሲናውዙም፤ ኮሽ ባለ ቁጥር ሲደነጋግጡ እዚህ ደርሰዋል። በሌሉበት ቦታ ሁሉ መልካሙን ነገር ሁሉ በፀርነት ፈርጀው ሲፈሩትም፤ ሲመነጥሩትም ኑረዋል። ታሪክ በቀደመ ህዝብ፤ አገርም በቀደም ህዝብ ዊዝደም ይሠራል።    ኢትዮጵያ አንጡራ ጠላቱ የሆነ