ልጥፎች

ከጁን 23, 2024 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ኑሩልኝ።

ምስል
  ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ ዓሊ የሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ሚር እያሉ እንዲህ ዓይነት በጎ ሃሳብ ሲያራምዱ ነበር። ያን በጎ ዕይታ ማን እንደዘረፈው አላውቅም። ስለ ሰዓት የምታሳልፍ የሥራ ባልደረባ እንዴት ማኔጅ ችግሯ ሊደረግ እንደሚገባ ሲገልፁ ዕንባዬ ፈቃዴን አልጠዬቀም። ያን ጊዜ የምታገለው ለድምፃአልባወች የኢትዮጵያ እናቶች ነበር። ሞቶዬ ያ ነበር። የተደገፋትም ለዛ ነበር። ግን የእኛ ነገር ………??? ስላበዛሁ ነው የጠፋሁት። ኑሩልኝ። @EliasMeseret «ኬንያውያን አዲሱን የሀገሪቱን የፋይናንስ እና ታክስ ህግ ተቃውመው ላለፉት ሶስት ቀናት ድምፃቸውን አሰሙ፣ ሰልፍ ወጡ፣ ህብረታቸውን አሳዩ ይህን ተከትሎ የኬንያው ፕሬዝደንት "ህዝቡ የሚለውን ካዳመጥን በኋላ ህጉ ላይ ለውጥ አርገናል፣ የሀሳብ ልውውጥ ስላደረግን ደስ ብሎኛል፣ ዴሞክራሲያችን እየሰራ እንደሆነ ማሳያ ነው" አሉ። በዚህ ያልረካው ህዝብ አሁንም ተቃውሞውን እያሰማ ነው። ተቃውሞውን ያሰማው የእኛ ህዝብ ቢሆንስ? - የሽብር ድርጊት ለመፈፀም በህቡዕ እንቅስቃሴ ሲያደርጉ - ከሀገሪቱ ታሪካዊ ጠላቶች ተልእኮ በመቀበል ሀገሪቱን የብጥብጥ ማዕከል ለማድረግ ሲያሴሩ - በድብቅ መሳርያ በማስገባት እና በገዳማት ጭምር ወታደራዊ ስልጠና በመስጠት ሲንቀሳቀሱ... ወዘተ ተብለው በጅምላ ወደ ማጎሪያ። አሳዛኝ ትውልድ።»