ልጥፎች

ከሴፕቴምበር 19, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ብልሃት የሌለው ቅላት በግራ ቀኙ ሲፈታተሽ።

ምስል
ተገፊው ማህበረስብ ዛሬም እንደ ትናንቱ ነገም…    „በሚያልፍ ቢዚህ ዓለም የምትኖሩ እናንተም መኳንንቱና ነገሥታቱን በሚገባ ሥራ ጸንተው የኖሩ ከናንተ አስቀድሞ የነበሩ አባቶቻችሁ እንደዚሁ መንግሥተ ሰማያትን እንደ ወረሱ ስማቸውም ለልጅ ልጅ ያማረ  እንደሆነ አሰቧቸው።“ መጽሐፈ መቃብያ ካልዕ ምዕራፍ ፲ ቁጥር ፳፯ „ኃኋ ከሥርጉተ©ሥላሴ 18.09.2018 ከጭምቷ ሲወዘርላንድ። ድሃን ስላስጠጋች ቅድስ ቤተ ክርስትያነችን ስትደፈር። https://www.zehabesha.com/amharic/archives/94354#respond ከሶማሌ ክልል የተፈናቀሉ የአማራ ክልል ተወላጆች በባህርዳር ከተማ ቤተክርስቲያን ደጃፍ በልዩ ሃይል ተደበደቡ https://www.youtube.com/watch?v=8shYma5YbO8 Ethiopia || የትግራይ ልዩ ሃይል አፍኖ እየውሰደ በደል እየፈጸመብን ነው Published on Sep 18, 2018 ·       ለምን? ዶር አብይ አህመድ እስቲ ይቆንጠጡ። „ለምን“ ቃሉ ፍልስፍና፤ ለማወቅ መሻት፤ ለመመርምር መፈልግ፤ ለመፍጠር መነሳሳትን ያመለክታል ... ቃሉ አቅም ይፈጥራል፤ ግርዶሽን ይገፋል፤ ጨለማን ያስወግዳል። „አይ“ ዕውነት ዕብለትን እንዲበቀለው አቅም ይለግሥሳል። ፍቅራዊነት መርሆ ጥላቻን ይበቀላል። ጥላቻን የሚበቀለው የትምህርት ዓይነት ቢኖር ፍቅራዊነት ብቻ ነው። ሥርጉተ ሥላሴ ስታድግ አይደለም ወላጆቿን፤ ሊቀ - ሊቀውንት አያቶቿንም፤ የቀለም መምህራኖቿን „ለምን“ ብላ ትጠይቅ ስለ ነበረ እድገቷም ዕውነትን በመፈለግ ላይ ያተኮረ ነበር። የንግግር ጥበብ መምህሬ ጋሼ አብነት ለምን መምህር ሆነህ ብላኮቦርድ እና ቾክ ትጠላለህ ብ