ልጥፎች

ከፌብሩወሪ 23, 2019 ልጥፎች በማሳየት ላይ

በምልስት ዕውነት እና ዘመኗ! ለጸሐፊ አቶ ወንድይራድ አሳማማው ጹሑፍ መልስ።

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ።  በምልስት ዕውነት እና ዘመኗ! „ እግዚአብሄርም አለ ፣ --- ሰውን በመልካችን እንደ   ምሳሌያችን እንፍጠር“ ኦሪት ዘፍጥረት ፩ ቁጥር ፳፮ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 23.02.2019 ከእመ ዝምታ - ሲዊዘርላንድ። መነሻ። https://www.satenaw.com/amharic/archives/64044 አብይ አህመድ – ጃዋር ሙሀመድ እና ሌንጮ ለታ – አንድም ሦስትም ናቸው ! ( ወንድይራድ አስማማው ) ሸር ያደረገው 658   February 22, 2019 ·        እፍታ። ውዶቼ እንዴት አላችሁልኝ? ደህና ናችሁ ወይ እኔ ከባለ ዕንባማዋ ከአላዛሯ ኢትዮጵያ ናፍቆት ከእናንተ ስስት በስተቀር ደህና ነኝ - አምላኬ ክብሩ ይስፋ። ትናንት አንድ  ጹሑፍ ሳተናው ላይ ተለጥፎ አነብብኩኝ። በዛው መድረክ መመሞገት ቢገባኝ ከእንግዲህ ቅኖችን ማስቸገር የተገባ ስላለሆነ በእኔ ብሎግ መጻፍ ግድ ብሎኛል። በምን ስሌት ጠ/ሚር አብይ አህመድን ጸሐፊው ከአባ ገዳ ጃዋር መሃመድ እና  ከአቶ ሌንጮ ለታ ጋር እንዳወደዱት የሚገርም ነው። ስለምን ዶር ለማን መገርሳስ ተዋቸው? ከቆረጡ ቆርጦ መጣጣፍ ነው። አባገዳ ጃዋር ሆኑ አቶ ሌንጮ ለታ ኦሮሞ ፈርስት ናቸው። በዛ ላይ ስለሰው ያላቸው አቋም የተከረኮመ ነው። ሰው ማለት ለእንሱ የኦሮሞ ደም ያለበት ብቻ ነውና። ቀድሞ ነገር „ኢትዮጵያ አገራችን“ ብሎውም አይቀበሉም። ወዳጆቻቸውም እንደ አቶ ንጉሡ ጥላሁን ዓይነቶቹ እነሱን እንዳይከፋቸው „አገሪቱ“ ነው የሚሉት።ለማማሻ ነው ያቺ መከረኛ የምትፈለገው፤ መላ የኢትዮጵያ ህዝብ ቢቃጠል፤ ቢነድ ኢትዮጵያ ምደረ በዳ ብትሆን አጀንዳቸው አይደ