ልጥፎች

ከፌብሩዋሪ 7, 2025 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ትንሽ ቆይታ ከጃዋሪዝም የአብይዝምን አቅላይነት ጎዳና ጋር ………

ምስል
  ትንሽ ቆይታ ከጃዋሪዝም የአብይዝምን አቅላይነት ጎዳና ጋር ………   "የቤትህ ቅናት በላኝ።"     #ጠብታ ።   ወርኃ የካቲት የታቦቴ የብላቴ ሎሬት ጸጋዬ ገ/ መድህን በስጋ የተለዬን ስለሆነ እያዘከርነው ቢሆን። ለ17 ዓመታት በዘለቀው በእምዬ ሲዊዘርላንድ በራዲዮ #ሎራ 97.5 መካከለኛ ሞገድ በወር ሁለት ጊዜ በዕለተ ሃሙስ በቀን ቅዱስ ከ15.00 -16.00 ጸጋዬ ራዲዮ በድንቁ አማርኛ ቋንቋ በሚተላለፈው መሰናዶ በአግባቡ በዬአመቱ ተከብሮ ይዘከራል። የራዲዮ ፕሮግራሙ የተመሰረተበት ዓላማም ግብም ይኽው ነውና። ለታላቅ ባለውለታ የቅኔ አባት መታሰቢያው ክብሩን፤ ልዕልናውን፤ የአማርኛ ቋንቋን የሥልጣኔ ትውፊቱን ማስቀጠል ነውና የትውልዱ ድርሻ።    #ውሽክታ ። አቶ ጃዋር መሃመድ ስለ አዲስ አበባ ሰሞኑን ያለው ቁምነገር አለ። ከዛ ያጎረፈ ሃሳቡ በፍፁም የተለዬ አዲስ አበባን የገነባትን #ጉራጌን አትዝለሉ ሲል ለኦሮሞ እና ለአማራ የአዲስ አበባ አቀንቃኞች መልዕክቱን ሳደምጥ #ቁጥር አንድ ውሽክ አልኩ። በነገራችን ላይ የጨመቱ ጉራጌ፤ ጋሞ፤ ወላይታ፤ አማሮ፤ አፋር ወዘተ ማህበረሰቦች ኢትዮጵያ ስለሰጣት ፈጣሪን አላህን ልታመሰግን ይገባታል።    ቁጥር ሁለቱ ውሽክታ ደግሞ በአገረ ጀርመን ላይ "እኛ መንግሥት መገልበጥ ሰልችቶናል" ሲል ውሽክ ብዬ ነበር። ኧረ በሞቴ አይሰልችህና ሞክረው በማለት መልሱንም ጥፌያለሁ። ሊንኩም ተቀምጧል።   ሰሞኑን ደግሞ በኦነግ ዓርማ በተንቆጠቆጠው አዳራሽ በአሜሪካ ኦሪንገን ላይ ተሰብሳቢወች በጀርባ በሚታዩበት የጃዋሪዝም ጉባኤ ላይ በኦሮምኛ ተናግሮ የተተረጎመውን " ማለዳ " በሚባል ዩቱብ ቻናል፤ "መንግሥት መገልበጥ ከሰለቸን ተሃድሶ ይባል፤ ተጠግኖ ተጠግ...

ከዬት ልጀምረው? #ዕውነት #ጋራጅ #አያስፈልገውም።

ምስል
  ከዬት ልጀምረው? #ዕውነት #ጋራጅ #አያስፈልገውም ።   "የቤትህ ቅናት በላኝ።"     ክፍል አንዱን ያዳመጡ "ልብ ወለድ ያሉት" አሉ። ልበወለድ ነው ብንል ጸሐፊው #የፋክት ልበወለድ ጸሐፊነቱን መካድ የሚገባ አይመስለኝም። እን በወርኃ ታህሳስ በ2019 የፃፍኩት እኮ አለሁኝ - በህይወት። ሂደቱን ብቻ ተመልክቼ። እንኳንስ ድርጊቱ በቁሙ በሚነበብበት፤ በሚተረጎምበት ወቅት ዛሬ ላይ። ሂደቱ ለሁሉም አይጠቅምም። #ክህደትም ነው። መታመንን የሰለቀጠ።    የሆነ ሆኖ ከሦስተኛ ወገን የሚመጡ ጉዳዮች ቅመማ ቅመም ሊጨማመርበት ቢችልም ጭብጡ ግን ፋክት ተኮር ነው። ጠንክረው የወጡ ተደጋጋሚ #ዝንባሌወች እንዳሉ ተመልክቻለሁኝ። አትኩረተ ኤርትራ፥ ነገረ ጎጃም እና ጎንደር። ጥቅሙ ግን አቅም መግቦት ላይ የባጁትም እራሳቸውን ይመዝኑበት። አባ ጎልጉል አቶ ሽመልስ አብዲሳ እኮ #እንቅጩን ተናግረዋል። "ኮንቢንስና ኮንፊይዝድ" በማለት። #ለ7 ወራት የማህበረ ኦነግ ጉዞ እንዳይደናቀፍ ታሽጎ ተቀምጦ በኋላ ወጣ። ከወጣ በኋላ ጥድፊያ ነበር የኮፒ ራይት። በዛ ውስጥ እምሽክ ስላለው የኢትዮጵያ ተስፋ ይሁን የአማራ ሰቆቃ ባለቤት አልባ ነበር።   ማህበረ ቅንነት ይመስላችኋልን አዲስ አበባ በፌድራሉ ሥር እንዳለች? #እእ ። እኔ ለአምስት ዓመታት ጽፌበታለሁኝ። ከመስከረም 5/2011 ጀምሮ አዲስ አበባ በኦሮምያ ሥር ናት። ለኦነግ የተገባው ቃል የኤርትራው ስምምነትም ይሄው ነው። ዶር ለማ መገርሳ እና ዶር ወርቅነህ ገበዬሁ ወደ ኤርትራ ሲጓዙ ዜና ነበር። ሲመለሱ #ፀጥታ ።    በወቅቱ ብሎጌ ላይ ጽፌበት ነበር። 5 የአዲስ አበባ ልጆች ተረሽነው፦ 1300 ወደ ጦላይ የተላኩትም ለኦነግ #ርችት ነበር። እስከ ...