ልጥፎች

ከኦክቶበር 30, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ቤተሰባዊ መሪነት ፍቅር በፍቅር ከስደተኛ ወገኖቹ ጋር። ተመስገን!

ምስል
ቤተሰባዊ መሪነት። „የሰው ልብ መንገድን ያዘጋጃል እግዚአብሄር ግን አካሄዱን የቃናለታል፤“ ምሳሌ ፲፮ ቁጥር ፱ ከሥርጉተ©ሥላሴ 30.10.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ።           አሁን ያገኘሁት ነው ጠ/ሚር አብይ አህመድ ጀርመን ርዕሰ መዲናው በርሊን ላይ የጠበቋቸውን ኢትዮጵያዊ ወገኖቻቸውን በፍቅር ተቀብለዋል። ያው ጠ/ሚር አይመስሉም ልክ አብሮ አደግ ጓደኛ ነው የሚመስሉት። መቼም የጀርመን መንግሥት ሳይገረመው አያቀርም።  ዕድሜ ልክ በመቃወም የኖረ ኢትዮጵያዊ ስደተኛ ዛሬ ከሙሴው ጋር እንዲህ በፍቅር እቅፍቅፍ ብሎ ሲሳም ሲታዩ እጅግ ያስደስታል። አብሶ ሥርጉትሻ ሐሴቷ ዝቀሽ ነው። አላሳፈሩኝም።   ባይበላም ባይጠጣም ጥሩ ነገር ነው እንዲህ ቤተሰባዊ መሆን። አብሶ ስደተኛ ብዙ ነገር አጥቶ ስለሚኖር መቼም ይህ የሰማይ ስጦታ ነው። ተመስገን።  እኔ ከስሜን አሜሪካውም ደመቅ ዓውድ ይልቅ ይህ በለጠብኝ አቀራረቡ እና ውስጣዊ እቅቅፉ ይሄ ላቀብኝ፤ የፈንሳዩንም አይቸዋለሁኝ የበርሊኑ ግን እኔ እንጃ ልክ የአገር ቤት ቤተሰባዊ ጠረን አለው።  ያው ከተደጋጋሚ ሞት እና አፈናም ወጥተው ነው ለ ዓይነ ሥጋ የተበቃው። እንደ ገና የመፈጠርም ያህል ነው። ብዙ የተከደኑ ነገሮች እዮር የሚያውቃቸው አሉና። ብቻ ተመስገን ነው። እስኪ ይጨርስለዎት! የኔዎቹ ኑሩልኝ። መሸቢያ ጊዜ።

ኮ/ ጎሹ ወልዴ ለአላዛሯ ኢትዮጵያ በምድሯ ሲገኙ ምርቃት ናቸው።

ምስል
ኮ/ ጎሹ ወልዴ ለአላዛሯ ኢትዮጵያ በምድሯ ሲገኙ እዮራዊ ምርቃት ናቸው። „ጥበብስ በቀደሙ ሰዎች ዘንድ ተመረመረች።“  መጽሐፈ ምሳሌ ፴፱ ቁጥር ፩ ከሥርጉተ©ሥላሴ  30.102018 ከጨምቷ ሲዊዘርላንድ። መልካም ነገር ኮ/ጎሹ ወልዴ አገር ቤት ገብተዋል። እንግዲህ በሳቸው ጥልቅ የማስተዋል አቅም የመጠቀም የጠ/ሚር አብይ ለማ ካቪኔ ጉዳይ ይሆናል። እጅግ ለረጅም ጊዜ፤ በተደጋጋሚ ጊዜም እንደምገልጠው ኮነሬሉ የተከደኑ የአገር ሲሳይ መሆናቸውን ነው።   እሳቸው የጠ/ሚር አብይ አማካሪ ከሆኑ ብዙ ነገር እንደሚቃለል ተስፋ አደርጋለሁኝ። የተወጣጠረው መተንፈስ የታሳነው አዬር ንጹህ አዬር ያገኛል። ኮነሬል ጎሹ ወልዴ ለአላዛሯ ኢትዮጵያ እዮራዊ ምርቃት ናቸውና ።  ምርቃትን መጠቀም ደግሞ የዘመኑ መሪዎች ልባምነት ልብ ብርሃንነት  ይወስነዋል።  አላዛሯ ኢትዮጵያ ከልቡ በሳል የሆነ፤ ልበ ሙሉ፤ ጨዋ ምርቁን የዋጠ፤ አማካሪ ያስፈልጋታል። ለዚህ ደግሞ ኮነሬል ጎሹ ወልዴ አብዝቶ የሰጣቸው የማድረግም፤ የመሆንም፤ የመቻልም፤ የመታገስም ባለሙሉ አቅመኛ ናቸው። እኛዊነትን ማግኘት የሚቻለበት አምክንዮ የውስጣቸው ማህተም ነው። ብሩህ ህሊናቸው እና ቅን አመለካከታቸው በራሱ አንድ ትውልድ ይገነባል። እኒህን የአላዛሯ ኢትዮጵያ አንጡራ ሃብት ኢትዮጵያ በ100 ዓመት ከማታገኛቸው ልዑቃን አንዱ ናቸው። ክውን፤ ሽክፍ፤ ጠፈፍ ያሉ ብርቱ እና ጠንካራ አብነትም መሆን የሚችሉ ደርባባ የፖለቲካ ሊሂቅ ናቸው። በወታደራዊው መስክ ሆነ በሲቢሉ በነበራቸው የተባ የተግባር ቆይታ፤ በስደትም አገር ቢሆን ክውን ያሉ ድምጣቸው ተሰምቶ የማይታወቅ የአገር ባለውለታ እና ተምሳሌት ናቸው። ስለሆነም እሳቸው የለውጡ አካልነታቸውን ከተበሰረ መዋለ ዕድሜ