ልጥፎች

ከጁላይ 17, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ፍቅር የጸሐይ መውጪያ እንጂ መግቢያ አይደለም!

ምስል
ፍቅር ዕዳ አይደለም። „አቤቱ አንተ ምህረትህን ከ እኔ አታርቅ ቸርነትህና እውነትህ ዘወትር ይጠብቁኝ!“ (መዝሙር ምዕራፍ ፲፩ ቁጥር ፴፰) ከሥርጉተ©ሥላሴ (ከኮሽ እይሏ ሲዊዝሻ) 17.07.2018 ·        መነሻዬ https://www.satenaw.com/amharic/archives/60747 „ የኤርትራው ዕርቅ ፈተና ይጠብቀዋል “ ይለናል ዋዜማ ራዲዮን፤   ዘሃበሻ እና ሳተናው ማዕዴ ናቸውና ከሳተናው ባገኘሁት ሁለት ጉዳይ ላይ የምለው ይኖረኛል። ሁለቱም ተያያዥ ባይሆኑም ተቀራራቢ ናቸው፤ ይሄኛው ትንሽ ከተስፋ ጋር ይገናኛል ሁለተኛው ግን ጨልምተኛ ነው።   „ የ ኤርትራው እርቅ ፈተና ይጠብቃዋል “ ፈተና አልባ ህይወት፤ ፈተና አልባ ኑሮ፤ ፈተና አልባ ነፍስ አይፈጠረም። ፈተና በአንድም በሌላም የኖራል። ፍቅር ደግሞ እንደ ተፈጥሮ አባልነቱ ተፈታኝ ነው። እንዲያውም የበዛው ፈተና   በእሱ እና በአርበኞቹ ላይ ነው። እንኳንስ ሰው አንሰሳት ነፍሳትም ሚዳቋ ከፈተና ለመዳን ነው ጉድጓድ እምትቆፍረው ... አሳን ለማጥመድ ነው መረብ የሚሠራው ...     ወደ ቀደመው ሰውኛ እና ተፈጥሮኛ ጉዳዬ ምለሰት ሳደርግ፤ የፈለገ ጫን ተደል ፈተና ይኖር የፍቅር ተፈጥሮ መርሆዎች ድል የማድረግ አቅማቸው ከሰውኛው በላይ ነው። በፍቅር ተፈጥሯዊ መርሆዎች ጥናት ለማድረግ ቢታሰብ የመዋለ ዘመን ክስተት መሆኑን መረዳት ይቻላል። ፍቅር ፈታኝ ሁኔታዎችን የሚፈታበት መሳሪያው በእጁ ነው ያለው።   ከሁሉ በላይ የፍቅር መርህ ተፈጥሯዊና ሰውኛ ስለሆነ ለቁስ፤ ለማተርያል፤ ለ

አብይ ኬኛ ለነባቢት ርትህኛ!

ምስል
የበደል ናፍቆት ግራጫዎችን አመሳቸው። „አህዛብን ገሠፅህ፣ ዝንጉዎችን አጠፋህ፣ ስማቸውን ለዘላለም ደመሰስህ።“ (መዝሙር ምዕራፍ ፱ ቁጥር ፭) ከሥርጉተ©ሥላሴ (17.07.2018) የአላዛሯ ኢትዮጵያ ክብር እዬጎላ መምጣት ያመማቸው እርኩሞች አሁንም እንደ ማህበረ ሳዖል በተለመደው የሴራ ገመዳቸው ኢትዮጵያን አቧራ ለብሳ የጥላሸት ጠቀራ መደብር ትሆን ዘንድ እዬታተሩ ነው። እራሱ ከዛ መከራ የወጣው አርበኛ ያ ሰቀቀን እናዳይደገም ይህ አብያዊ መንፈስ የዘላለም የፈወስ መንገድ እንዲሆን ከማበረታት ይልቅ ጨዋታው ሌላ እና ሌልኛ ሆኗል። ያ የሚያንገፈግፍ እና የሚያነዘፈዝፍ የ27 ዓመት መከራ ደግሞ ይመጣ ዘንድ በቀለኞች አጋጣሚውን አግኝተው የልባቸውን ይወጡ ዘንድ ቅዱሱን የአብይ መንፈስ ብስጩ እና ገርጭራጫ በማድረግ የተለመደ የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት እዬታተሩ ነው። በዚህ ሁኔታ የታሰበው የሽግግር መንግሥት ዕውንነትን ለማምጣት ነው ትልሙ። ግን ለአንዱም ሳይሆን ፈሶ ይቀራል። እርስ በርሳቸው መተማመን አይደለም ሰላምታ እንኳን የማይለዋወጡ ናቸው።  በአንድ ከተማ እዬተኖረ በአንድ የነፃነት ማዕዶት መስዋዕትነት እዬተከፈለ አንዱ ሌላውን ሲያደባ፤ ሲሰልል፤ ሲያሳድም ነው የኖረው። ዛሬ ይህ በምድር ሊሆን ይችላል ተብሎ የማይታሰብ ቅናዊ ንጹህ ቅዱስ መንፈስ ወደ ፊት መጥቶ ሁሉንም በመፈውስ እርምጃ ሲጀመር የለመደባቸውን የጭካኔ እሾሕ ሰራሽ ሸንክነታቸውን በ አንድም በሌላም እአስተዋል ነው። ያን ገመና እንደ ተሸከሙ ሌላ ሴራ በደባ በመምራት እንደገና በምንትሶ፤ በቅብርጥሶ ድርጅት እዬተባለ አዲሱ ወጣት ደግሞ ተለቅሞ እስር ቤት ገብቶ የድርብ ጥቃት ሰለባ እንዲሆን እዬተፈለገ ነው። የአገሬ ልጆች የበፊቱ