#የአገር መሪን የሥልጣን ጊዜ ስለመገደብ የእኔ ዕይታ። "ላም አለኝ በሰማይ ወተቷን የማላይ።"
#የአገር መሪን የሥልጣን ጊዜ ስለመገደብ የእኔ ዕይታ። "ላም አለኝ በሰማይ ወተቷን የማላይ።" "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን። #ምዕራፍ ፲፱። ብዙ ተቃዋሚወች ይሁኑ ተፎካካሪወች ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድን አቅልሎ የማዬት የወል ባህሪ አይባቸዋለሁ። ልምድ እንደሌላቸውም ሲናገሩ አድምጫለሁኝ። በቂ ልምድ አላቸው። ሚሊተሪ ላይ ሠርተዋል፤ በተመድ ፕሮጀክት ተሳትፈዋል፤ ከኢንሳ መስራችነትም አሉበት በዛው ተቋም መሪነቱም ታክሎ ልምድ ይገበይበታል፤ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂን በሚር ደረጃ መርተዋል፤ የኢህአዴግ የፓርላማ አባል ነበሩ፤ በኦሮሚያ የተለያዩ ኃላፊነቶች ላይ ሠርተዋል። ይህ በቂ ነው። የኢትዮጵያ መሪ ከሆኑ በኋላ እሳቸው የሚያምኑበትን መስመር ተግተው ነው የሚሠሩት። ቢሮክራሲው ላይ የሉበትም መስክ ላይ፤ ፕሮጀክት ተኮር ጉዳዮችን ይወጥናሉ፤ ይፈጽማሉም። ዳሽ የሆነው ሰብአዊነት ላይ ነው የማጽናናት፤ አይዟችሁ የማለት፤ በተከፋት ቀዬ በህዝባቸው ውስጥ ተገኝተው ጥግ የመሆን አቅም አለመኖር። እስር ላይ ያለው የማይገፋ ተራራ። ሌላው ዳሽ የሆነው የቢሮ አስተዳደራዊ ሥራም ነው። በተጨማሪም የሌሎችን መከፋት #አቅለው ማዬታቸው፤ ለመፍትሄው አለመትጋታቸው ዳሽ ነው። ጠቅላይ ሚር መለስ ዜናዊ የትኛው ተቋም ላይ ሠርተዋል? ከጫካ ህይወት ቤተ- መንግሥት። በቃ! ዕውነቱ ይሄ ነው። ያለውን #ዕውነት #ማስከፋት አያስፈልግም። ከዚህም ሌላ መሪነት ፈቃደ እግዚአብሄር፤ ቅብዓ ስለመኖሩም ማመን ያስፈልጋል። የሆነ ሆኖ አገራዊ ምክክሩ ለምን እንዳስፈለገ፤ ከዛ በፊት ለሙከራ አቋቁመው ያፈረሷቸው ኮሚሽኖች ሁሉ በመደዴ ታስበው የተከ...