ልጥፎች

ከጁን 20, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ትውልድ የማይተካቸው ኮ/ ጎሹ ወልዴ ቃላቸውን አተሙ!

ምስል
ትውልድ ማይተካቸው ኮ/ ጎሹ ወልዴ  ዛሬ ለኢትዮጵያ ህዝብ ዓለም አቀፋዊ ጥሪ አቀሩቡ።  ቃላቸውንም በኢትዮጵያዊነት                  አተሙ! ከሥርጉተ ሥላሴ 20.06.2018 (ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ።)                             "በመከራዬ ሳሉ ወደ አምላኬ ወደ እግዚአብሄር ጮኽሁ፤                                                  እርሱም ሰማኝ፤"                                   (ትንቢተ ዮናስ ምዕራፍ ፪ ቁጥር ፫)   ትወልድ የማይተካቸው ኮ/ ጎሹ ውልዴ ዛሬ በውጬ እና በአገር ውስጥ ለሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያወያነ ሁሉ ለጠ/ ሚር አብይ አህመድ ሙሉ እግዛ እና ለቀናዊ ጉዟቸው ጥንካሬና ብርታት እንዲሆናቿው ለኢትዮጵውያን በሙሉ ታላቅ ዓለም ዓቀፋዊ ታሪካዊ ጥሪ አስተለላፉ።  እኒህ ታላቅ ሙሁር እና የፖለቲካ ሊሂቅ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ሰንደቅዓላማ ናቸውም ማለት እችላለሁኝ። ከአገር ከወጡ በኋዋላ መድህን የሚባል የፖለቲካ ድርጅት መሥርተው ካደራጁ በኋዋላ በራሳቸው ፈቃድ ለተተኪ ወጣቶች ያደራጁትን መድህን ፓርቲ ያሰረከቡ የመጀመሪያው የፖለቲካ ሊሂቅ ናቸው። ውስጣቸው ብቃታቸው ዕንቁ ነው። እኔ በልጅነት ኮ/ አሳፋ ሞሲሳ የሚባሉ ከፍተኛ መኮነን ይሆልታ ግንተ ዋና አሰትዳዳሪ ስለክቡርነታቸው እያስጠኑኝ ነበር ያደኩት። ስለሆነም በውስጤ የበቀሉ የፖለቲካ ሊሂቀ ሊሂቃን ናቸው ማለት እላለሁኝ። እንደ ዕድል ሆኖም ክቡርነታቸውን የተኳቸውን ወጣት ሁልት ረ/ ፕሮፌሰሮችንም በአካል ተገናኝቼ ተወያይቼም ነበር። ሁልጊዜ ስለ ብቁ የአገር መሪ ሲታሰብ አስባቸዋለሁኝ። በደርግ ዘመን  ዓራት ዓይናማ ቁልፍ አካል ነበሩ። ሳይመቻቸው ሲቀር ወደ አሜሪካ

የአፍሪካ ቀንድ ታላቅ የምሥራች ቀን ዋዜማ!

ምስል
የአፍሪካ ቀንድ ታላቅ የምሥራች ቀን ነው።  የበርሊኑ ግንብ የተደረመሰበት ዋዜማ! የረጋ ወተት ቅቤ ይወጣዋል።    ከሥርጉተ ሥላሴ 20.06.2018 (ከገዳማዊቷ - ሲዊዘርላንድ)                  "የሰው ልብ መንግድን ያዘጋጃል፤ እግዚአብሄር ግን አካሄዱን ያቃነለታል።" (ምሳሌ ምዕራፍ  ፲፮ ቁጥር ፱)   ዋዜማ። መቼም በዬዕለቱ አበረታች ብቻ ሳይሆን አጽናኝም፤ ተስፋም፤ የምህረት መንገድም፤ የፍቅር ጉዞም ተጀምሯል። በተደጋጋሚ እንደ ገለጽኩት ፈቀደ እግዚአብሄርም ነው። ኢትዮጵያን በቀሽ ብሏታል ፈጣሪ አምላክ። የመላ ኢትዮጵያ ህዝብ ጸሎት፤ እንባ እዬርን አንኳኳ፤ በሩን አስከፈተ፤ ፈጣሪም በቃልኪዳኑ ልክ ሙሴ ሰጠን። ይህ የፍቅር ሙሴ ጥበቡ ስልቱ ከፈጣሪው የተሰጠው ነው። በቅንነት ላገልግላችሁ ብሎ ተነሳ፤ እኛ ቅነንታችን በድርቅ ተመቶ ባንደግፈውም፤ እኛ ቅኖች ሆነን አይዞህ ለማለት አቅም ቢያነሰንም ጥንካሬው የፈጣሪ ነውና ይሄው እንደ ጥረቱ ዛሬ ታላቅ የአፍሪካ ቀንድ ሆነለት። ማዕለተ አብይ! ተመስገን! እኔ የሚናፍቀኝ የበርሊኑ የመረቡ ግንቡ ሲናድ የኤርትራ ህዝብ እንዴት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚነጉድ ነው። ምክንያቱም የስንት ዓመቱ ውጊያ እና ውጤቱን መሬት ላይ ኑሮበት አይቶታል እና። ፍቅርን ስትቀርበው ፍቅርን ስትቀበለው እንዴት እንደሚያበራ። ፍቅርን ስትሸሸው ፍቅርን ስትገፈትረው ደግሞ እንዴት አጭር፤ ኮስማና፤ አመዳም እና ቡላ እንደሚያደርግ፤ መለዬት ናፍቆት አይደለም። መለዬት ከሞትም በላይ ነው። ዛሬ የልደት የፋሲካ የትንሳኤ ዕለት ነው። እትዬ አልጋነሽ በሩ የተከፈተ ዕለት ጎንደር ቀጥ ብላ ሄዳ እናቴን እንደምታይ ነው። መቼም በዚህ ውስጥ ስንት የዕንባ ሲቃ እንደሚወርድ ነው።

ሃኪሙ የኢትዮጵያ ጠ/ ሚር፤

ምስል
     ፍቅር ኪሎኛ አይደለም።                                    ከሥርጉተ ሥላሴ 20.06.2018 (ከገዳማዊቷ ' ሲዊዘርላንድ።)                  „በጎ ነገር ከጥንት ጀምሮ ለበጎ ሰዎች ተፈጠረች እንደዚሁ ክፉ ነገርም ለሃጢያተኞች ተፈጠረች“                                       (መጽሐፈ ሲራክ ምዕራፍ ፴፱ ቁጥር ፳፭) ፍቅር የቁጥር ተማሪ አይደለም። ወይንም ፍቅር በሜትር የሚመተር አይደለም። ወይንም ፍቅር በወቄት የሚለካ አይደለም። ወይንም ፍቅር በክንድ የሚሰፈር   አይደለም። ወይንም ፍቅር በእፉኝ // በጭብጦ የሚመዘንም አይደለም። ፍቅር ኪሎ የለውም። በፍቅር ተፈጥሮ ውስጥ ቀመር የለም። ፍቅር መለኪያ መስፈርት የለውም። ፍቅርን ሲያስቡት ቀላል ተፈጥሮ ይመስላል። ግን እንደ ፍቅር እጅግ ፈተኝ እና አድካሚ ተፈጥሮ የለም። ፍቅር ውስጥ በቀላል ውጣ ወረድ ወይንም በለብለብ ግጥምጥሞሽ የፍቅርን ተፈጥሮ ማግኘት ይቸግራል። ፍቅር ችግር የሚሆነው ሰው መሆን ሲያቅት ብቻ ነው። ሰው መሆን ያቀተ ዕለት የፍቅርን ተፈጥሮ ፈተናዎችን ተራራ አክለው፤ ምን ተራራ ብቻ ውሃ ያዘለ ተራራ ሆነው ሳንሸከመው ግን በሃሳብ ብቻ የዝዝላል። ፍቅር ጀግና አይደለም የሚፈልገው ለእኔ። ስለምን ? ፍቅር ራሱ ጀግና ስለሆነ። እርግጥ ነው ጀግና ጀግና ቢፈልገው አይደንቅም፤ ግን ጀግናን ፈጣሪው ጀግና ስለሆነ ነው ፍቅር ጀግና አይደለም የሚፈልገው ያልኩት። ፍቅር ጥላቻን አሸናፊ ሆኖ ሲፈጠር ነው የጀገነው። ጀግ