ልጥፎች

ከፌብሩዋሪ 3, 2025 ልጥፎች በማሳየት ላይ

#ውስጤን በስሱ።

ምስል
  #ውስጤን በስሱ።    "የቤትህ ቅናት በላኝ።"       እንዴት አደራችሁ ክብሮቼ። ውስጤን ብጥብጥ ያደረገው ግፋዊ እርምጃ ስከታተል አንድ ጹሁፍ አገኜሁኝ። ሰማዕቱ አልፏል። ነገስ ነው ጥያቄው። በስሱ ሁለት ዓመት ሊቃረበው ያለው ትግል እና ሂደቱን እስኪ እንቃኜው። ብዙ ቻልኩ፤ ብብዙም ታገስኩኝ።    ዘጋቢው አቶ ይክበር ይመስገን በ6 ወር ብቻ 87 #ንጹኃን ተገድለዋል ባይ ናቸው። የገዳዮችን ግምታቸውንም አስቀምጠዋል። ጦርነት ውስጥ #በቀል #ቂም ምግቡ ነው። እናም የአማራ እናት ተሰቃዬች። ይህ ባህርዳር ብቻ ሳይሆን ከወሎ ደሴ ሃይቅ - ኮንበልቻ - ወልድያ ከተሞች ውጪ ያሉ የአማራ ከተሞች ማርቆስ፤ ዳንግላ፤ ፍኖተሰላም፤ ደብረታቦር፤ ጋይንት፤ አዲስ ዘመን፤ ዳባት፤ ደባርቅ፥ አዲስዘመን፤ ወረታ፤ አይከል፤ ጎንደር ከተማም በመሰሉ ከተሞችም ግፍ ይፈፀማል። ፌድራሉ ከህወሃት ጋር በደቡብ አፍሪካ ስምምነት ሲያደርግ ደስታዬ ወደር አልነበረውም። አፈሙዝ ፀጥ ሲል የከተማ ነዋሪወች እረፍት ታዬኝ።   የሆነ ሆነኖ የፋኖ ንቅናቄው የተጀመረው #ከተማ ላይ ነበር። ግራ ነበር የተጋባሁት። ቀደም ብሎ ከዚህም ከዚያም እንድሳተፍ ያወያዩኝ ነበሩ። የማይታሰብ ነገር። በህይወቴ አንድ ጊዜ ብቻ ነው የድርጅት አባል የሆንኩት። ድርጅቴ ሲፈርስ በቃ። መለካለክ ከሌላ ጋር ሰብዕናዬ አይፈቅድም። በምን ቋንቋስ ልንግባባ??? ወደፊትም የዬትኛውም የፖለቲካ ድርጅት አባልም አካልም አልሆንም። ፈጽሞ።    ወደ ተነሳሁበት ጉዳይ ስመለስ የሽምቅ ውጊያ እኔ በታሪኬ ከተማ ውስጥ ከመደበኛ ሰራዊት ጋር ፊት ለፊት ሲገጥም ያዬሁት አሁን ነው። ከተማ ላይ ሽምቅ መሪወቹ እነ ሻለቃ ዳዊትየተገኜውን ድል ዘገባ ሲ...

መልካምነት ለየካቲት 1.2017

ምስል
 

የአማራ እናት ዘመኗ መቼ ይመጣ ይሆን?

ምስል
  የአማራ እናት ዘመኗ መቼ ይመጣ ይሆን? "የቤትህ ቅናት በላኝ።"   ፀጥ ብሎ ህግ አክብሮ ቢሰራም #መገደል ። እታገላለሁ ቢልም #መሰዋት ። እማራለሁ ሲል #መታገት ። እኖራለሁ ሲል #መጨፍጨፍ ። ብቅ ሲል #መጨፍለቅ ወይ #መጠለፍ ። አንደበቱን ሲገልጽ #ካቴና ። የመከራው ሁሉ የምትሸከም ምስኪኗ የአማራ እናት፤ እህት፤ አክስት ሚስት። ወይንም የትዳር አጋር። ትግሉ በዬፈርጁ የሁሉ መዳረሻ መከበሪያ፤ መሞገሻ፤ ቢላ ቅንጡ ቤት እና ሥልጡን መኪና መግዣ፤ ወይ መሸለሚያ መሞካሻ፦ ለሰብዕና ግንባታ። እና የአማራ እናት #ዘመኗ መቼ ይመጣ ይሆን???? የልብ አድራሿዋ ጥቃት አውጪዋስ ማን ይሆን???? ይህን መከራ አስቀድሞ መታገል ወይንስ እንደ ቄራ ሥጋ ለቅርጫ ማብቃት????? ከአቶ ደጀን ፔጅ ነው ያገኜሁት። ሰሞኑን ጠቅላይ ሚር አብይ ቶርች አላደረግነም እያሉ ይደሰኩራሉ። የአዲስ አበባው የቢላ ቤት እስር ቤታቸው የግላቸው አይደለምን? ወለሉ በደም የጨቀዬ ስለመሆኑ ያፈኗቸው እኮ ገልፀውልናል። ይህስ ምስኪን የአማራ ባንክ ሰራተኛ አቶ ኢሳያስ በላይ በምን ህይወቱ አለፈ ይሆን? ሞጋች የለወት???? ድብልቅልቅ፤ ቅይጥይጥ ስላለ ድሮ እንሞግተወት የነበረው ይስከን ብለን እንደ ሳይለንት ማጆሪቲው ፀጥ አልን። ግራ ቢገባን። የጠራ የትግል መስመር ቢኖር ግን ሃሳብ ያለው የለም የሚሉትን ዲስኩሮወትን #እንጦርጦስ የሚልክ ሃሳብ አመንጭተን መቀናጣተወትን #ቅስሙን በሰበርነው። ግን አቅጣጫው ባለዬለት ትግል አቅም ማፍሰሱም ሆነ መድከሙ ትርፍ እና ኪሳራው ተመዝኖ #ተጠሞን ። እንጂ እርስወ እራሰወት አባል ሳይሆኑ #በውራጅ አባላት ይህን ያህል መዋለ ንዋይ ጊዜ ሲባክን ዝም - ዝም - ዝም ባልተባሉ። "የደብረማርቆስ ሪፈራል ሆስፒታል የቆዳ ስፔሻሊስት የ...

የእኔ ዕይታ እና የሌሎችም። #የአዳኝ ባተሌ አባት ነፍስ እንደ ዋዛ መንገድ ላይ መቅረት። #መራራ ስንብት። እንደ አልባሌ #ዕውቀት ለባሩድ??? #ልቅና ለበቀል???

ምስል
  #የአዳኝ ባተሌ አባት ነፍስ እንደ ዋዛ መንገድ ላይ መቅረት። #መራራ ስንብት። እንደ አልባሌ #ዕውቀት ለባሩድ??? #ልቅና ለበቀል??? "የቤትህ ቅናት በላኝ።"      ሃኪም ለእኔ #ነብይም #መላእክም ነው። ለምን ሃኪም #በጭካኔ ይገደላል? ሃኪም ሩህሩህ ሰባእዊ እና አዛኝ ፍጥረት ነው። ለምን #አረማዊ ነገር ይፈፀምበታል? ህይወታችን የቀጠለችው እኮ በእነሱ ድካም ነው። ከፈጣሪ በታች እረዳታችን የመኖራችን ጌታወች እኮ እነሱ ኒቸው። በእጅግ አሳዛኝ ዜና ነው። የጉበት፤ የቆሽት እና የሃሞት ከረጢት እስፔሻሊስቱ ዶር አንዱአለም ዳኜ ከአንዱ ሆስፒታል ወደ ሌላ ሆስፒታል ነፍስን የመታደግ ቅዱስ ተግባር እዬባተሉ በነበሩበት ከመኪናቸው አስወርደው እንደተገደሉ ነው ዜናወች የሚያመለክቱት። እስከ መቼ ነው #የአማራ እናት፤ የአማራ #እህት ፤ የአማራ #ሚስት ፤ የአማራ #አክስት ፦ የአማራ #ምራት ፤ የአማራ ልጆች ተስፋ የባሩድ #ቀለብ ሆነው የሚቀጥሉት? የጭካኔ ፉክክር ለየትኛው ማህበረሰብ እድገት ይሆን የሚጠቅመው? የአማራ ልጅ ቀጣይ ህይወት #የዝብሪት ቤት ነው የሆነው? እባካችሁ #አደብ ግዙ እና #ቁጭ ብላችሁ ምክሩ። ከመገዳደል የሚያተርፈው ሰይጣን ብቻ ነው። #አዳኝ እንዴት ይገደላል? በዬትኛውም አለም ሃኪሞች ቀስ ብለው ሲራመዱ እንኳን አታዮዋቸውም። ሁልጊዜ ጥድፊያ ነው። ሰውን የማትረፍ፤ ለሰው ችግር ፈጥኖ የመድረስ ጥድፊያ። ለመሆኑ ከዚህ ሙያ ለመድረስ ስንት መዋለ መንፈስ አገርስ፤ ማህበረሰብስ? ቤተሰብስ አፈሰዋል? መምህርም እኮ ናቸው። የብዙኃን #አባ ። መዳህኒትም ፈዋሽ ናቸው። ያቺን የጭንቅ ሰዓት እኮ ሁላችንም እናውቃታለን። ሃኪም ባይኖር በህይወት ማን ይቀጥል ነበር። አንድ ጣሊያናዊ ሃኪም በኮረና ዘመን ...