ልጥፎች

ከፌብሩወሪ 11, 2023 ልጥፎች በማሳየት ላይ

እንደ ጠርሙስ ጭንቅላታቸውን ከሰከሱት፤

ለመናገር ሳይሆን ለማድመጥ ጊዜ ይኑረን። ልመና ነው። • https://www.youtube.com/watch?v=c6CMNXJ3BP8 EOTC TV | ወቅታዊ ጉዳይ | ደም ረግጠው ገብተው ፎቶ ይነሳሉ እንዴት ነን? አቅም አገኛችሁ ይሆን? አይዟችሁ። "ከመከራ በስተጀርባ ታላቅ ክብር አለ" "እንደ ጠርሙስ ጭንቅላታቸውን ከሰከሱት፤ ሌሊቱን ሙሉ ከተማይቱን በማዘጋጃ ቤት ፅዳተኞች አፀዱት፤ ሽታው አያስቀርብም፤ ዬተገኙት፤ ያሉትን ለመለዬት ሄደን ለማፅናናት ይፈቀድልን፤ ጥቃቱ ሦስት ነው ታግቶ ስንቅም መፀዳዳትም ዬማይፈቀድለት፤ ከዬቤቱ እዬታፈሰ ዬት እንደተወሰደ ዬማይታወቅ፤ በጅምላ ዬሚገደል፤ ዬሚቆስል፤ ዬሚደበደብ …… ከሌላ ቦታ አምጥተውደፋበት ……" ዕድምታውን አዳምጡት። አቅም ዬለኝም ለመሥራት። "የመከራን ቀን እጠብቃለሁ።" ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 09/02/2023 ቸርነትህን አበራክትልን፤ ምህረትህንም ላክልን። አሜን።  

ዬማተቤ ድምፅ ብቻ መሪዬ ነው።

ዬማተቤ ድምፅ ብቻ መሪዬ ነው። "ኢትዮጵያ ነነዌ ናት። ዕውነት ማብራሪያ አይሻም። ዕውነት እራሱ በቂ ነው። ያለ ደም መስዋዕትነት አለ። ሥራ አታብዙብን። ያለብን መከራ ይበቃናል። "በኢትዮጵያ ውስጥ ዬጥቁር ቀን ታሪክ ተጽፏል።" (ብፁዑ አባታችን አቡነ ጴጥሮስ።) • https://www.youtube.com/watch?v=tuwl_GsfHv0 EOTC TV | "ወቅታዊ ጉዳይ | የሴራ ፖለቲካ አያዋጣም" ከጽናት ጉልላት ዬኢትዮጵያ ቅድስት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ድምጽ በስተቀረ ሌላ ለማድመጥ አንፍቀድ። መሪ አለን። ሙሴ አለን። እረኛ አለን። መሪ፤ ሙሴ፤ እረኛ ያለው የሃይማኖት ሰው ድምፁን የሚያገኜው ከማተቡ ብቻ ነው። አዳምጡት። በዛ መስመር እንጓዝ። መረጃውን ማሰባሰብ ጥሩ ነው። ጉዟችን ቀያሽ ግን ዬኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ብቻ ልትሆን ይገባል። ጋዜጠኛ፤ ፀሐፍት፤ ዬፖለቲካ ተንታኝ ለገኃዱ አለምነው። ለመንፈሳዊ ሕይወት ሚስጢረ ጥምቀት ነው ብርኃናችን። ቅድስታችን ፕሮፖጋንዲስት፤ ማኒፌስቶ፤ ካቢኔ አይደለችም። የሐዋርያት መሠረት እንጂ። ድምፀ ተዋህዶ ከኢትዮጵያዊው ቅዱስ ሲኖዶስ ብቻ። እግዚአብሄር ይስጥልኝ። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 09/02/2023 የብፁዓን ቅዱሳን አቨው ፀሎት እና በረከት ይደርብን። አሜን።  

#ለዘዋራ ሰብዕና ዬድፍረት ሐጢያት ያሰምጣል። #ለአሳቸው እና ለዘዋራው ለጠቅላይ ሚር ነው መልዕክቴ።

  #ለዘዋራ ሰብዕና ዬድፍረት ሐጢያት ያሰምጣል። #ለአሳቸው እና ለዘዋራው ለጠቅላይ ሚር ነው መልዕክቴ። #ሳናይ አምነን #ስናይ ተቀጣን። "ከንቱ ዬከንቱ ከንቱ ሁሉ ነገር ከንቱ።"   ሄሮድስ ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ ንቅንቅ ሳይል በትረ ሥልጣኔ ይቀጥላል ብለው በጨቀጨቅ መጪ እያሉ ነው። አሳቻነታቸው መስታውት ሆኗል። የሰው ልጅ ደም ለዛውም ሙሉ አምስት አመት ወደ እዮር ይላካል። ፈለጉትም አልፈለጉትም። አሁን ባለው ሁኔታ እሳቸው ፈብርከው ከሚፈጥሩት ቀውስ ውጪ አንድም ነፍስ ያለው ተቋም ቀርቶ አሰባሳቢ አጀንዳ ያለው የፖለቲካ ድርጅት ዬለም። ሁሉንም ፈጥፍጠው አፍዘውታል።   የተዋህደው ተዋህዷል፤ ዬተንከረፈፈው ጠርዝ ላይ ተንጠልጥሎ ኮሽ ባለ ቁጥር እዬተጣመረም እዬተሰባሰበም የመግለጫ ሲሳይ ሆኗል። በሳቸው ዘመን እንኳንስ የዓለምኔ ፖለቲካ ዬሚመጥን አቅም ያለው ተፎካካሪ የፖለቲካ ድርጅት ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለለብ ማውጣት አይታሰብም። ምክንያት አንደኛው ሰላይ ናቸው። ሁለተኛው በተፈጥሯቸው ዬተዥጎረጎሩ ሁነው ዬተፈጠሩ ናቸው።    ዬዓለሙን ሎሬት ሽልማት ከመውሰድ በላይ ድል ዬለም። በጨካኝ ሥርዓት ተወልገው አድገው ወስደዋል። እራሳቸው አስመራጭ ኮሜቴ ሆነው ፕሬዚዳንት ዬሚል ሥያሜ ቀርቶ ነበር ጠቅልለዋል። እሳቸው አይታመሙም፤ አካላቸው አይጎድልም፤ ድምፃቸው አይዘጋም፤ ዬምንም ዓይነት አደጋ አይደርስባቸውም። ዘሊለማዊ ናቸው። ዕሳቤያቸው ይህ ነው።    ዬሚያስታግሱን ሰጥ ለጥ ካደረጉ በኋላ በዬቤቱ እዬዞሩ በዶላር የሚያማልሉትን በዶላር፤ በስልክ ዬሚያማልሉትን በስልክ፤ በሽምግልና ዬሚያማልሉትን በሽምግልና፤ በብክል ዬሚሸኙትን በብክል፤ ለካቴና ዬሚሰጡትንም እንዲሁ። ኢትዮጵያ መዳፋቸው ውስጥ ናት። አባ ቶርቤ መሃንዲስ፤ አስተናጋጅ፤ ሃኪም፤ ነጋዴ፤ ተ

አባ ገብረ ሚካኤል ፈንቴ

ምስል
  ለበረከት ክብሮቼ ተሽቀዳደሙ። "ሰለማይነገር ሰጦታው እግዚአብሄር ይመሰገን አባታችን ተገኝተዋል እኔም ከእንግሊዝ በርኒግሀም እኛው ለእኛው መደራጇ መሀበር ካገኝሁት ብር ላይ 10 ሺ ብር ሰጥቻቸዋለው አባታችንን ለመርዳት ለማገዝ ከፈለጋቹ ይሄ ትክክለኛ ሰልካቸው እና የባንክ አካውንታቸው ነው አባታችን ህክምና ያሰፋልጋቸዋል 0912137799 ሰልካቸው ነው አባ ገብረ ሚካኤል ፈንቴ 1000200837936 ንግድ ባንክ ዳይ ወደ መርዳትና ሼር ወደ ማድረግ ሱራ የኪዲዬ ልጅ " "ዬቤትህ ቅናት በላኝ።" "አባታችን አባ ገብረ ሚካኤል ፈንቴ ህክምና ጀምረዋል። ቅዱስ ኡራኤል ኪሊኒክም ሙሉ ወጭውን ችሎላቸው ህክምና ማድረግ ችለዋል። አባታችንን ለመርዳት ለማገዝ ከፈለጋቹ ይሄ ትክክለኛ አካውንታቸው እና ስልካቸው ነው ደዉሉላቸው፤ 1000200837936 ንግድ ባንክ አባ ገብረ ሚካኤል ፈንቴ 0912137799 ሰልካቸው ነው።"……… ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 09/02/2023 አቤቱ ሃጢያታችን በርክቷል እና ምህረቱን ላክልን።     " ዝም ብዬ ዬመከራን ቀን እጠብቃለሁ" በመከራ ቀን ደግነት ይንገሥ። ዬተከበሩ ዶር ዳንኤል በቀለ እባከወት መታመናችን አይካዱት። እባክወትን። ይህን ቃለ ወንጌል ለረጅም ጊዜ ተጠቅሜበታለሁኝ። አንዲት ብሩክ እህቴ ለመነችኝ። ለእሷ ስል አስታገስኩት። እሷ መቼ ትግል እንደ ጀመረች አላውቅም። ዬእኔው በጥዋቱ ሆነ እና ዘመኔን በዕንባ ሸኜሁት። ውስጤ ዬሚለኝን ነገር ሳልቆጥብ፤ ዬዘመኑን የፖለቲካም ባህሬ፤ ዬሄሮድስ ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ ያልተገለጠ ተቆጥቦ እዬተመነዘረ ጥቅም ላይ የሚውለው ተለዋዋጭ ሰብዕና፤ ኢትዮጵያ ከተፈጠረችበት ዘመን ያለውን ክፋ ነገር ሁሉ ሪባይዝ በማ

መንፈሳዊ የሐዘን ቀን በብሄራዊ ደረጃ አዲስ አበባ ሰላማዊ ሰልፋ ይቻላንል? ኦሮምያ ክልል ከፈቀደ ብቻ። ይህ ለብዙወቻችሁ መርዶ ሊሆን ይችላል።

  መንፈሳዊ የሐዘን ቀን በብሄራዊ ደረጃ አዲስ አበባ ሰላማዊ ሰልፋ ይቻላንል? ኦሮምያ ክልል ከፈቀደ ብቻ። ይህ ለብዙወቻችሁ መርዶ ሊሆን ይችላል። "ዬቤትህቅናት በላኝ።" በጣም ለረጅም ጊዜ ጽፌበታለሁኝ። አዲስ አበባ ላይ ምንም ዓይነት ህዝባዊ ንቅናቄ በአደባባይ አይፈቀድም። ምክንያቱ ከፔጄ ላልቆያችሁ ለአዲሶቹ መርዶ ሊሆን ይችላል። እንደ ሥርጉተ ዕይታ ከመስከረም 05/2011 ጀምሮ አዲስ አበባ ዬኦሮምያ ክልል ሆናለች። ኦህዴድም፤ ኦፌኮም መግለጫ ሰጥተውበታል። ዬፌድራሉ መንግሥት ማስተባበያ አልሰጠም። አልገሰፁም። ለምንኢትዮጵያ ስለተጠለፈች። አዲስ አበባ ውስጥ ያሉ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ፤ ፌድራላዊ ተቋማትም ተጠሪነቱ ለኦሮምያክልል ነው። መርዶ ነው ይሄ ዬማይታዬው እኮ ጠቅላይ ሚሩ ከኦሮምያ ዬመጡ ስለሆነ አይታያችሁም ዕውነቱ። አባይ በጣና ላይ፤ ጣና በአባይ ላይ ተዋህደው ሲኖሩ አይታይም። ልክ እንደዛ ነው። ማንኛውም ብሄራዊ ክንውን በዋዜማው የኦሮምያ ፕሬዚዳንት ወጥተው ይናገራሉ። ለምን? ጠቅላይ ሚሩ አንድ ነገር ቢሆኑ ዬሚተኩ እሳቸው ስለሆኑ ነው። ደቡብ ሲሄዱም ይዘዋቸው ነው ዬሚሄዱት። በ2011 ዬፃፍኩት ነበር አዲስ አበባ ከውጪ ሲገባ በቢዛ ይሆናል ብዬ። ለምን የያዙት አቅጣጫ ያ ስለሆነ። ለአፍሪካም አስጊ ነው። አንድ ሆቴል የምስራቅ አፍሪካ ባህል ማዕከል በኦሮምያ ዬሚል አዳምጫለሁኝ። ለነገሩ በ2019 ታህሳስ ላይ ለአፍሪካም አስጊ መሆኑን በድፍረት ጽፌበታለሁኝ። ከሁሉ በላይሄ ሮድስ ጠሚአብይ አህመድ ዘዋራም፤ አሳቻም ናቸው። ብዙ ግሎባል ፍላጎቶችን አከማችተው ለመፈፀም ሁሉ ዲታ ሆነዋል። ይህን ያልተረዱ ሰብዕናወች ምርኩዛቸው ናቸው። አሁንም አቅጣጫእዬሰጡበብፁዓን ቅዱሳን አባቶቻችን ላይ እስር እንዲኖር ዬአቅጣጫ በር ሲከፍቱ ተመልክቻለሁኝ።

የዬካቲት 5/2015 ህዝባዊ መንፈሳዊ ሰልፍ ቅድመ ሁኔታው ካልተሟላ ይካሄዳል ዬሚል መንፈሳዊ መግለጫ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ተሰጥቷል።

የዬካቲት 5/2015 ህዝባዊ መንፈሳዊ ሰልፍ ቅድመ ሁኔታው ካልተሟላ ይካሄዳል ዬሚል መንፈሳዊ መግለጫ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ተሰጥቷል። ትናንት ማምሻ ላይ የኢትዮጵያ መንግሥት ዬሰጠው መግለጫ ዬኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ምላሽ ሰጥታለች። በፆመ ነነነዌን ምህላ ዬንስኃ ፀሎት መጠናቀቁን ተገልጧል። ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍንም በሚመለከት ቅድመ ሁኔታወች ካልተሟሉ ዬቀጣይ ዬህልውና ተጋድሎም እንደሚቀጥል አቅጣጫ ተስጥቷል። እናዳምጥ። ከልባችን ሁነን። ፀሎቱ፤ ምህላው፤ ሱባኤው በፈቃድ መቀጠል ይገባል። ከ30 በላይ የሆኑ ሰማዕታትን አስባለች። ፍትኃቱ እንደሚቀጥልም አስገንዝባለች። ዬተጎዱትንም ለመጠገን፤ ለማፅናናትም ፈቃድ መታጣቱን ቅድስቷ ገልፃለች። አዳዲስ ቅዱሳን ሰማዕታት ማግኜቷን ቤተክርስትያኗ መጽናናትን ማግኜቷ ገልፃለች። ቅድስታችን ግልፅ እና ቀጥተኛ ጥበባዊ መካች ትሁታዊ አቋምን ገልፃለች። የክልል መንንግሥታዊ አስተዳደርን አድንቃለች ሱማሌ፤ ቬንሻንጉል፤ ደቡብ ምዕራብ፤ ደቡብ፤ ድሬደዋን፤ ሀረሬ፤ አፋር፥ ሲዳማን አስተዳደሮችን አመስግናለች። ሌሎች ተቋማትንም ትብብራቸውን ለገለፁ ዬኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ሃይማኖት ዕውቅና ሰጥታለች። ህገ ወጦችን ዕውቅና በመንግሥት ዕውቅና መሰጠቱ፤ ዬተሰጠው መግለጫም ቅድስት ቤተክርስትያናችን አለመቀበሏን በሃዘን ገልጣለች። ቃላት አጠቃቀሙም መልካም አለመሆኑ ገልፃለች። #መግለጫው ። መንፈሱ ……… ለኢትዮጵያ መንግሥት …… በደላችን ለዓለምዓቀፋ ማህበረሰብ ለማሳወቅ ተገቢውን ጥበቃ እንዲያደርግልን መፍቀድ ወይንም ያቀረብነውን ቅድመ ሁኔታ ማሟላት እንጂ ሰማዕትነታችን ደስ ብሎን እንቀበላለን። ልጆቻችን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የታሠሩ እንዲፈታ፤ ካሳ እንዲከፍል ለበደለው፤ አገር አቀፍ ሰልፋችን በራሳችን አደ

የዶ/ር ወዳጄነህ መልዕክት‼️

ምስል
ምስክርነት። ተመስገን። የዶ/ር ወዳጄነህ መልዕክት "እኔማ የኢትዬጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያንን የማውቃት ይመስለኝ ነበር። ባለፉት ሦስት ቀናት እንደተረዳሁት ግን ስላንቺ የነገሩኝ ሰዎችና መጻህፍት ሁሉ ካለሽ ክብር፣ ሞገስና ዝና ከፊሉን እንኳን እንዳልነገሩኝ ነው። ተዋህዶ ሆይ!" "ንፁህ እምባ፣ ጥልቅ ትህትና፣ ብርቱ ትዕግስት፣ ታላቅ ጥበብ፣ ብዙ እውቀት፣ ሰፊ ማስተዋል፣ የሚያስፈራ ግርማ አየሁብሽና ተገረምኩኝ፣ ልቤ ተደነቀ፣ እጄን በአፌ ላይ ጫንኩኝ! የጸሎትና የምልጃሽ እጣን የልዑል እግዚአብሔርን ቤተመቅደስ ሲያጥነው፣ ዙፋኑን ሲያውደው ማየት እንኳን እኔን ደካማውን ሰው ይቅርና ቅዱሳን መላዕክቱን ያስደንቃል።" " በነቢዩ በዳንኤል መፅሃፍ እንደሚነበብ እጅ ያልነካው ድንጋይ ከሰማይ ወርዶ ሳይፈርስ ፣ ሳይከፈል፣ ሳይቆረስ ታላቅ ተራራ ሆኖ ጸንቶ እንደኖረ አንቺም በኢትዮጵያ ምድር ላይ ታላቅ ተራራ ሆነሽ ለአፍሪካ ትምክህት፣ ለመላው አለምም ክብር ሆነሽ ትኖሪያለሽ። ከእግዚአብሔር የተማሩት፣ ትሁታንና ብሩካን የሆኑት፣ ማቅ የለበሱልሽ የተወደዱ ልጆችሽ እንዴት የታደሉ ናቸው! ከሩቅ እያየሽ የሚወድሽና የሚያከብርሽ ዶ/ር ወዳጄነህ መሐረነ"  

ክርስትና ወደ ኢትዮጵያ የገባው በ4ኛው ዓ.ም የዛሬ 2019 ዓመት

በሉ እንግዲህ የምትወዱኝ አንብቡ የምትጠሉኝ በግዜ ጥፉ! ተቀራራቢ ትርጉም ኮፒ 1. የመጀመሪያዎቹ ጋላዎች (ኦሮሞዎች) ጣዖት አምላኪዎች፣ የአምልኮ ዛፎች፣ ወንዞች፣ ተራራዎች፣ ፀሀይ፣ ጨረቃ እና ከዋክብት ነበሩ፣ እና ብዙዎቹ ጋላዎች እስከ ዛሬ እነዚህን ያመልካሉ። ለእነዚህ አማልክት እንስሳት፣እህል፣እቅፍ አበባ እና የደም መስዋዕት ያቀርባሉ።ሃይማኖታቸው እንስሳዊ ነው።በአባይ ወንዝ ምንጭ ላይ ያሉ ነዋሪዎች ወንዙን ያመልኩታል፣እልፍ ከብቶች ደግሞ ለምንጩ መስዋእት ያቀርባሉ። ኮፒ 2. ጋላዎች ወደ ኢትዮጵያ የገቡ የቅርብ ጊዜ ስደተኞች ናቸው።ጋላዎች እራሳቸውን በጋላስ ስም አይጠሩም ነገር ግን እራሳቸውን ኦሮሞ ብለው ይጠሩታል።በ15ኛው መቶ ክፍለ ዘመን እንደኖረ የሚነገርለት ኦሮሞ የሚባል ቅድመ አያት እንዳላቸው ይናገራሉ።ኦሮሞ ኃያል አለቃ ነበረ። ስምንት ወንዶች ልጆችም ነበሩት። ኦሮሞ እና ልጆቹ በመጀመሪያ በአፍሪካ ደቡባዊ ሞቃታማ አካባቢዎች ይኖሩ ነበር እና ተባዝተው ታላቅ ሀገር ሆኑ። እራሳቸውንም ኦሮሞ ብለው ይጠሩታል ምክንያቱም ኦሮሞ ማለት "ጠንካራ ወይም ጎበዝ" ማለት ሲሆን ጋላ ማለት ደግሞ "ወራሪዎች ወይም መጤ" ማለት ነው። .............................................................................. ይህንን ፅሁፍ ከሁለት ዓመት በፊት አውጥቸው ነበር።ፅሁፉን ያወጣሁበት ግዜ የዘመነ #NoMore ዋዜማና እኔም ጁንታነት ማዕርግ የተሰጠኝ ግዜ እነ ዘር ለገበሬ ኢትዮጵያኒስቶች ያየሉበት አምልኮተ አብይም ከአምልኮተ ተዋህዶ. ኦርቶዶክስነት ለብዙው ሰው በልጦ ሰማየ ሰማያት የተሰቀለበት ግዜ ስለነበር ከጥቂት ሰዎች በስተቀረ ጉዳየ ያለው አልነበረም። ፅሁፉ በኦሮሞዎች እንደማይወደድ አው

ትምህርተ ጵጵስና።

ምስል
ትምህርተ ጵጵስና። ያልተቋረጠው የእስከንድሪያው መንበረ ማርቆስ ስልጣነ ክህነት (apostolic succession) ቅብብሎሽ ይሄ ነው ። 1. ማርቆስ 2. አንያኖስ 3. ሜልያስ 4. ክርዳኑ 5. አምብርዮስ 6. ዮስጦስ 7. አውማንዮስ 8. መርክያኖስ 9. ክላውያኖስ 10. አክርጵያኖስ 11. ዮልዮስ 12. ድሜጥሮስ 13. ያሮክላ (ሔራክልስ) 14. ዲዮናስዮስ 15. መክሲሞስ 16. ቴዎናስ 17. ጴጥሮስ (ተፍጻሜተ ሰማዕት) 18. አኪላስ 19. እለእስክንድሮስ 20. አትናቴዎስ 21. ጴጥሮስ 2ኛ 22. ጢሞቴዎስ 23. ቴዎፍሎስ 24. ቄርሎስ 25. ዲዮስቆሮስ 26. ጢሞቴዎስ 2ኛ 27. ጴጥሮስ 3ኛ 28. አትናቴዎስ 2ኛ 29. ዮሐንስ 30. ዮሐንስ 2ኛ 31. ዲዮስቆሮስ 2ኛ 32. ጢሞቴዎስ 3ኛ 33. ቴዎዶስዮስ (ቴውዳስስ) 34. ጴጥሮስ 4ኛ 35. ድምያኖስ 36. አንስጣስዮስ 37. አንድራኒቆስ 38. ብንያሚን 39. ያቃቱ (አጋቶን) 40. ዮሐንስ 3ኛ 41. ይስሐቅ 42. ስምዖን 43. እለእስክንድሮስ 2ኛ 44. ቆዝሞስ 45. ቴዎድሮስ 46. ካኤል (ሚካኤል) 47. ሚናስ 48. ዮሐንስ 4ኛ 49. ማርቆስ 2ኛ 50. ያዕቆብ 1ኛ 51. ስምዖን 2ኛ 52. ዮሳብ 1ኛ (ዮሴፍ) 53. ካኤል (ሚካኤል) 2ኛ 54. ቆዝሞስ 2ኛ 55. ስንትዮ 1ኛ 56. ሚካኤል 1ኛ 57. ገብርኤል 1ኛ 58. ቆዝሞስ 3ኛ 59. መቃርዮስ 1ኛ 60. ታውፋኔዎስ 61. ሚናስ 2ኛ 62. አብርሃም 63. ፊላታዎስ 64. ዘካርያስ 65. ስንትዩ 2ኛ 66. ክርስቶዶሉ (ገብረ ክርስቶስ) 67. ቄርሎስ 2ኛ (ጌርሎስ) 68. ሚካኤል 2ኛ 69. መቃርዮስ 2ኛ (መቃርስ) 70. ገብርኤል 2ኛ 71. ሚካኤል 3ኛ 72. ዮሐንስ 5ኛ 73. ማርቆስ 3ኛ 74. ዮሐንስ 6ኛ 75. ቄርሎስ 3ኛ 76. አትናቴዎስ 3

#ምዕቷ እና ሐዋርያነቷ።

ምስል
#ምዕቷ እና ሐዋርያነቷ። አቶ አዬለ ግዛው እንደፃፋት። "በደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት ዳሰነች ወረዳ በማኅበረ ቅዱሳን አስተባባሪነት በዳሰነችኛ ቋንቋ ቅዱስ ወንጌልን ሲማሩ ከነበሩ ወገኖች መካከል 1182 አዳዲስ አማንያን ብጹዕ አቡነ ፊልጶስ የደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት እና ብጹዕ አቡነ ኤልያስ የስዊድንና እስካንዲናቪያን ሀገረ ስብከት ሊቀ-ጳጳስ በተገኙበት በኦሞ መድኃኒዓለም ቤተ ክርስቲያን ሥርዓተ ጥምቀት ተፈጽሞላቸው የቅድስት ሥላሴን ልጅነት በማግኘት የቤተ ክርስቲያን አባላት ሆነዋል፡፡ EOTC " እንዴት አደርን። ቅድስቷ እንዴት አደረች። ወስብኃት ለእግዚአብሄር።  

#የጤና ባለሙያዎች እንደሚሉት ጠ/ሚሩ ሶስትአይነት የአዕምሮ እክል አለባቸው።

ምስል
" #የጤና ባለሙያዎች እንደሚሉት ጠ/ሚሩ ሶስትአይነት የአዕምሮ እክል አለባቸው። Bipolar Disorder Delusion of Grandiosity ADHA(attention deficit hyperactivity disorder) ➫Bipolar Disorder ➫it's abrain disorder that causes mood swing means its not about thinking "positive enough" or snapping out of it or about "negative feeling" በተለምዶ የባህሪ ወይም የሙድ መቀያየር ማለት ነው። አቢይ አህመድ የሆነ ሰዓት ላይ በጣም መልካም ለመምሰል ሰዎችን ያበላል ፣የአሮጊት ቤት ይሰራል፣ በተቃራኒው ደግሞ ሌላ ቦታ ላይ የድሀና የለፍቶ አዳሪ ቤት በዶዘር ያፈርሳሉ። ያ ሁሉ ሰው በማንነቱ ምክንያት ሲታረድ ለምን? ተብለው ሲጠየቁ አሜሪካም ሰው ይማታል ይላሉ። ይህ አይነት የአዕምሮ በሽታ #bipolar disorder ይባላል። ➫Delusion of grandiosity means entitlement superiority የምንለው ሲሆን ራስን አዋቂ እና የበላይ አድርጎ የመቁጠር በሽታ ነው። #አቢይ አህመድ የሆነ ሰዓት ላይ ኢንጅነር ነኝ ብለው ስለ እንጦጦ ፓርክ አሰራር እና ዲዛይን ያብራራሉ ፣ሌላ ጊዜ ደግሞ አርቲስቶች ን #ኖታ ካለስተማርኩ ዞር ስትል ስለወንጌልና ስለ ቁራን እኔ ነኝ አዋዊ ይላሉ። ይህ #Delusion of grandiosity ምልክት ነው። ➫ADHA(attention deficit hyperactivity disorder) means trouble coping with stress and childish activity ማለት እንደ ህፃን መሆን መንቀዥቀዥ አንዱን ሳይጨርሱ ሌላው