ልጥፎች

ከጁን 18, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

የኢትዮጵያ ህይወት።

ምስል
ጥሩ ሰው ሰፊ ስብዕና። ከሥርጉተ ሥላሴ 18.06.2018 (ከጭምቷ - ሲዊዘርላንድ) ዳዊትም፣--- ሥራውን ሁሉ ምሳሌ አውቅ ዘንድ ይህ ሁሉ በእግዚአብሄር እጅ ተጽፎ መጣልኝ አለ። (መጽሐፈ ዜና መዋእለ ምዕራፍ ፳፰ ቁጥር ፲፱) የታደለ ማህጸን። የታደለ አብራክ። የታደለ እትብት። የታደለች መሬት። ኢትዮጵያ ብርሃን ወጣላት። ኢትዮጵያ ፈጣሪ አምላክ በቃሽ አላት። በቃ ራስ እግሩ ቅንነት። ራስ እግሩ ፍቅር። ራስ እግሩ መሆን። ራስ እግሩ ቁም ነገር። እራስ እግሩ ምህረት። ራስ እግሩ ማቀራረብ። ራስ እግሩ ማግስታዊነት። ራስ እግሩ ሰዋዊነት። ራስ እግሩ ተፈጥሯዊነት። እንዲህ ዓይነት የተባረከ የተቀደስ ብቁ መንፈስ የሰጠን አምላክ የተመሰገነ ይሁን። አሜን! ይህ ማለት ግን በሁሉም ሃሳብ ተሰማምቻለሁ ማለት አይደለም። የልዩነት ሃሳብ ያለው እንኳን ቢሆን በፍቅር አስማምቶ፤ አዋዶ ህሊና በጎ እንዲያስብ፤   ህሊና መልካምነትን እንዲያመርት፤   ህሊና ንጹህ የታጠበ እንዲሆን፤   የሚመክር - የጎበጠን ለማቃናት የሚያግዝ ግን ኮስታራ፤ ግን ወንዳ ወንድ፤ ግን ሃሞት ያለው፤ ግን የቆረጠ እናቱን ብቻ ሳይሆን አፍሪካን አንድ ለማድረግ የሩቅ ህልመኛ። የአፍሪካ ህዝብ ደስ ብሎት፤ ስቆ አድሮ መዋል እንዲችል እጅ ለእጅ ለማያያዝ የሚተጋ ጥሩ ሰው ሰፊ ልቦና፤ መጠነ ሰፊ ራዕይ ያለው። ሰፊ ሆድ፤ ሰፊ ስብዕና ያለው። ኧረ ከዓይን ያውጣህ መዳህኒተ ዓለም አባቴ የሚያሰኝ።   የሰው ልጅ የማይመች ሃሳብም ቢሆን ደስ ብሎት ለመቀበል የሚያስችል ባለ አቅም። ሃሳቡን ባትሸምቱ

የድጋፍ ሰልፍ አዲስ አባባ ላይ ጦሱ መከራ ነው።

ምስል
ፍቅር የልብ እና የውስጥ እንጂ የፖስተር አይደለም? ከሥርጉተ ሥላሴ 18.06.2018 ከገዳማዊቷ ሲወዘርላንድ። „ … ከዚህም በላይ ደግሞ የአምላኬን ቤት ስለወደድሁ ለመቅደሱ ካዘጋጀሁት  ሁሉ ሌላ የግል  ገንዘቤ  የሚሆን ወረቅና ብር አለኝ እና ለአምላኬ ቤት ሰጥቼዋለሁኝ።"          (መጽሐፈ ዜና መዋዕለ ቀዳማዊ ምዕራፍ ፳፱ ቁጥር ፫ - ፬ ) እኔ ለጠ/ ሚር አብይ አህመድ የድጋፍ ሰልፍ አስፈላጊ ነው ብዬ አላምንም፤፡ ምክንያቱም አጋጣሚውን የሚጠብቁ የሰለጡኑ እኩይ የግራ ዘመም መንፈሶች ስላሉ ። ይልቅ እኔ የማስበው ዕድሉ ያለችሁ እንደ እኔ ማዕቀብ የማይጣልባቸው ወገኖቼ በቴሌቪዥን፤ በጹሁፍ፤ በራዲዮ ለወያኔ ሃርነት ትግራይ የስንቅ ቋት የሆኑ ሃሳቦችን ወጥቶ መሞገት ሰፊው ድርሻ ይሆናል። አዋሳ ላይ እኮ የሆነው ይሄው ነው። አድብተው ጠበቁ፤ ሲቆሰቁሱ ካራረሙ፤ አጋጣሚው ሲገኝ ግራቀኙ እኩይ መንፈስ ህውከቱን ፈጠሩት። በሰው ልጅ መከራ የአብይ አስተዳደርን ለማስወቀስ ሄዱ። ዋሽንግተን ፖስት የጻፈበት ፊርማ ሳይደርቅ ነው ይሄ የተከናወነው። ለጠ/ ሚር አብይ አህመድን እኮ አቀባበል ሲያደርግ የደቡብ ህዝብ ብሄራዊ ቀን ነበር። ደረጃው ታይቶም ተሰምቶም አይተወቅም። ልክ የኬኒያ መንግሥት ያደረገውን ነው አዋሳ የፈጸመው። ያን ቀን እኮ ሥራ ሁሉ ዝግ ነበር ብዬ አስባሉሁኝ። አክብሮቱም፤ ደስታውም ልክ አልነበረውም የውስጥም ነበር፤ ሥርዓቱም አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ነበር። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶው አባት " ከነፍሴ አዳምጥኩዎት" ነበር ያሉት፤ ሌላው የስብሰባው ተሳታፊ "እንቅልፍ የተኛሁት የእርስዎን ሹመት ካዳመጥኩኝ በሆ ዋላ" ነበር ያሉት። ሌላውም አቶ አባተ ደግሞ ፡በሰላም ቤቴ ገብቼ

ወይ ባህርዳር እንደ ውጪ ወራሪ ጠላት ..?

ምስል
ወይ ባህርዳር እንደ ውጪ ጠላት የመርዝ ጭስ መሞከሪያ? ከሥርጉተ - ሥላሴ 18.06.2018 (ከገዳማዊቷ - ሲዊዘርላንድ) "በሥጋው ቁርበት ላይ ቁስል ቢሆንና ቢሽር በቁስሉም ሥፍራ ነጭ እባጭ ወይም  ቀላ ያለ ቋቁቻ ቢወጣ በካህኑ ዘንድ ይታያል"   (ኦሪት ዘሌዋውያን ምዕራፍ ፲፫ ቁጥር ፲፰– ፲፱።) ማዘን ለማለት እንደ ሰውነት ብቻ ሳይሆን ከዛም በላይ ነው። በዓለም ዓቀፍ ፍርድ ቤት የሚያስጠይቅ መከራ ነው ባህርዳር ላይ የተፈጸመው። አንድ ወጣት ሙሁር የዩነቨርሲቲ ሙሁር ሲናገር በታቀደ ሁኔታ ከተማ ላይ ሊተገበር የማይገባው የጥቃት ዓይነትን ነው የባህርዳር ሰማዕታት ያስተናገዱት። ወደ ኋዋላ በምልስት ለምን ሆነ ለሚለው ምክንያታዊ የሆነ ነገር አለው። በአንድ ከይሲ ዕሳቤ ሰርጎ ገብቶ ያስፈጸመው ተልዕኮ መሆኑ ከመቀድሙ ለማገናዘብ እኔ በግሌ ተረድቻለሁኝ። ሚዲያ ላይም ጥንቃቄ የለም። የትኛው እሳቤ ህዝብን ለበለጠ ጥቃት ይዳርጋል የሚለው ማንዘርዘሪያ የለውም። የሰው ልጅ ህይወት ከሸቀጠም ባነሰ ደረጃ የተገመተበት ዘመን ነው በግራው ፖለቲካ ፍልስፍና፤ ጊዚያዊ እንጂ ዘላቂ ሁኔታዎች አይጠኑም። በማስተዋል ሊመረመሩ የሚገባቸው ነገሮች ጎልተው ይወጣሉ በቃ የፈረደባት የ ኢትዮጵያ እናት ብርንዶ ታቀርባለች። ወሸኔነቱ በማመላላጥ ከጎንደር የአማራ ተጋድሎ ጋር ተዛብቶ ቀረበ፤ ያ ቀደመ ዕልቂቱ ተከተለ ያው በመሞኮሪያው ህዝብ ላይ። ስለሆነም ይህ የተቋጠረ የበቀል እርምጃ ገፊ ገረጭራጫ ሃይል  ነበረው ። እነሱ ነፍሳቸውን አያውቁትም ይህን መሰል ዱብ እዳ ይመጣል ብለው።   በዚህ ከይሲ እና በቅጡ በታቀደ ከራስ ቃር አቀራርቦ በተሰጠ ትንተና   ገፊ ሃይል ጫ