ልጥፎች

ከኤፕሪል 18, 2024 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ አሊ እግዚአብሄር አቦይ ስብኃት ነጋን፤ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂን፤ ሻለቃ ዳዊትን እንዲጠራላቸው ተማፀኑ። #የአብቹ ላንቃ መልዕክት ልኳል።

ምስል
  ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ አሊ እግዚአብሄር አቦይ ስብኃት ነጋን፤ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂን፤ ሻለቃ ዳዊትን እንዲጠራላቸው ተማፀኑ። #የአብቹ ላንቃ መልዕክት ልኳል።     ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና በህይወት እያለ ይህን ይሰማ ዘንድ ፈቃዱ ስለሆነ ፈጣሪ ይመስገን።   እኔ በአብይዝም እና ህህዋቲዝም ጦርነት ካወገዙት በጣት ከሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊ ዜጎች አንዷ ነበርኩኝ። ሰቢዕዊ ቀውሱን ብቻ ነበር እምዘግበው። እንዲያውም ደስታችሁን በልክ ያዙት ምክንያቱም ሌላ ደስታ ስታገኙ መደርደሪያ እንዳይጠባችሁ፤ ከዚህም ሌላ ደስታችሁን ስትነጠቁ የሥነ ልቦና ህመም ተጠቂ እንዳትሆኑ፤ ይህም ብቻ ሳይሆን ደስታ ሲበዛ ፈጣሪ ይከፋ እና ምርቃት ያነሳል በማለት ስሞግትም ነበር የመቀሌ ተያዘ ርችት ጊዜ። አቶ ሻንቆ የሚባሉ ጥሩ ወዳጄ በጣም ይከፋብኝ ይሞግቱኝም ነበር። ዛሬ ያለውን ነገር ሁል በዝርዝር አስቀድሜ ጽፌዋለሁ ልቦና ላላቸው ወገኖቼ። አቅምም አላባከንኩም።    ህወሃት ቤተ መንግሥቱን ፈቅዶ ከለቀ ጀምሮም በህወሃት ላይ አንዳችም ነገር አልፃፍኩም። የከፋኝ አማራ ክልል እና አፋር ክልል ላይ የፈፀመው በደል ነበር፤ እንጂ የአብይዝም ካድሬወች ውሃ በቀጠነ ህወሃትን ሲያብጠለጥሉት አቅም አላባከንኩም ፈቅዶ መንበረ ሥልጣንን ከማስከበር ሌላ ምን ይምጣላችሁ በማለት ነበር የሞገትኩት። ለዛውም ለእኔ ስለ ህወሃት ሆነ፤ ስለ ሻብያ ቀስቃሽም፤ ፕሮፖጋንዲስትም አያስፈልገኝም። በጦርነት ቀጠና ውስጥ ስለአደኩ ሁሉን በደል አውቀዋለሁና።   የሆነ ሆኖ ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ አዲሱን ዓዋጅ አውጃዋል። ለሰማዩም ዳኛ ውሰድልኝ ብለዋል። የአብይዝም እና ህወሃቲዝም ጦርነት ሆድዕቃው ጊዜ ራዲዮሎጂ ነው እና እያዬን ነው። እያዳመጥን ነው።   #ቁርጡ ።   #የኢትዮጵያ ፌድርሽን ምክር ቤት፤ #የኢትዮጵ

ስለምን መነጣጠል? መከራን የመድፈር፤ የመቀበል። መከራን ፈቅዶ የመሸከም፤ በመከራ ሐሴት አግኝቶ መከራን ስለማስተዳደር ለፈቀዱ ቀንበጥ ወጣቶች ልዩነት መፍጠር መታመም ነው። ድዌ ነው። በሽታ ነው። ወጣቶቹ ምን አበሳጫቸው? ስለምን ይህን እርምጃ ለመውሰድ ተገደዱ?

ምስል
  ስለምን መነጣጠል?       መከራን የመድፈር፤ የመቀበል። መከራን ፈቅዶ የመሸከም፤ በመከራ ሐሴት አግኝቶ መከራን ስለማስተዳደር ለፈቀዱ ቀንበጥ ወጣቶች ልዩነት መፍጠር መታመም ነው። ድዌ ነው። በሽታ ነው። ወጣቶቹ ምን አበሳጫቸው? ስለምን ይህን እርምጃ ለመውሰድ ተገደዱ? ይህን አገር እመራለሁ የሚለው ማህበረ እህዲድወኦነግ ሊመረምረው ይገባል። በቀል ዘርግቶ ህዝብ አዳምን እያስጨነቀ መከፋቱን የበለጠ ባያቆሳስለው ስል ላሳስብ እወዳለሁኝ።   እነኝህ ሦስት ወጣቶችም ሆኑ ሌሎችም በስቃይ ላይ የሚገኙ ወጣቶች የዘመን ሚስጢር ናቸው። ሁሉም ምን እያደረገ እንደሆን የሚመዝን የችሎት ተግባር ነው የፈፀሙት። በዚህ ጉዳይ ላይ ተራ የኮፒ ራይት ትርምስ መፍጠር ሳይሆን ሰክኖ እራስን መመርመር፤ እራስን ማድመጥ፤ እራስን ቡርሽ ገዝቶ ማረም ይገባል። እንጂ በሰፈር በአጥቢያ ተተልትሎ ማሰብ አይገባም። ከፍ እና ዝቅ ማድረግም አይገባም። አንድ ሰው ለአመነበት ተልዕኮ ህይወቱን ከመስጠት በላይ ምን ያድርግላችሁ? ጀግና ከሆኑ ሁሉም ጀግና፤ ሰማዕት ከሆኑም ሁሉም ሰማዕት። እንደ ዘራዕይ ደረስ፤ እንደ አብርኃም ደቦጭ፤ እንደ ሞገስ አስገዶም ። አታበላልጡ። ከፍ ዝቅ አታድርጉ። አትነጣጥሉ። አትለያዩ። በአፈፃፀሙም አትሻሙ። ወጣቶቹ ህሊናቸው የፈቀደውን ወስነው ፈጽመዋል።    ሌላው ትግሉንም አታነጣጥሉት ይህ ከሀምሌ ፭ ጀምሮ የህሊና ማህበራዊ ብቃት ክንውን የደረሰበት የእድገት ደረጃ በሂደቱ ከሀ እስከ ፐ በጽናት ቁመው የመሩ ያታገሉ ብቻ ሳይሆን የህዝባዊ ተሳትፎም አጠቃላይ ውጤት ነው። የአንድ አገር ልጅነት ርዕሰ መዲና፤ መንበረ መንግሥት መቀመጫ አለኝ የሚለው ሊኖረው ይገባል። ድንቅነሽ ባዕት ሊኖርት ይገባል። የዘመናት መስዋዕትነት የወል ማዕዶት አናት ያስፈልጋል። የኢትዮጵያ፤ የአፍሪካ