ልጥፎች

ከኤፕሪል 24, 2019 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ሽብር በአዋሳ እና የመንግሥት ዝምታ (አቶ ዳሞ ጎታሞ እንደጻፉት // ጸሐፊ አቶ መስፍን እንደ ተረጎሙት።)

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ  ሽብር በአዋሳ                 እና   የመንግሥት ዝምታ „ ሳቅን እብድ ነህ፤ ደስታንም፤ --- ምን ታደርጋለህ ? አልኩት። “   መጽሐፈ መክብብ ፪ ቁጥር ፪ ፀሀፊ፤ ዳሞ ጎታሞ (Damo Gotamo) ትርጉም፤ መስፍን ማሞ ተሰማ                     ህም!ድንቋ ፍልቅልቋ አዋሳ ምን ታጭቶልሽ ይሆን? እም! የሲዳማ ፅንፈኞች የአዋሳን ህዝብ ማሸበር ከጀመሩ እነሆ ዓመት ሆናቸው። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ወደ ሥልጣን ከመምጣታቸው አንድ ዓመት በፊት መንግሥታዊ ሥልጣናቸውን ተጠቅመው ሲዳማ ያልሆነውን ህዝብ ያስፈራሩና ያዋክቡት ነበር፤ አሁን ደግሞ በግላጭ የከተማዋን ህዝብ ማሸበርና አካላዊ ጥቃት ወደ መፈፀም ተሸጋግረዋል። ዘግናኝ ወንጀሎችን እየፈፀሙ የሚጠይቃቸውም በሌለበት የሥልጣን ከለላ ውስጥ ይኖራሉ። ባለፈው ዓመት በፍቼ ጨምበለላ በዓል ወቅት የሲዳማ ፅንፈኞች ሰዎችን ከነነፍሳቸው አቃጥለዋል፤ በሺዎች የሚቆጠሩትን የከተማዋን ነዋሪዎች አፈናቅለዋል። የወላይታዎችን መኖሪያ ቤቶች አውድመው ንብረቶቻቸውንም ዘርፈዋል። ይህንን ወንጀል የፈፀሙ ሽብርተኞች አሁንም በህብረተሰቡ ውስጥ የተናኙ ሲሆን ተጨማሪ ወንጀሎችንም እየፈፀሙ ናቸው። ከጥቂት ወራት በፊት አሸባሪዎቹ ሲዳማ ያልሆኑ የህብረተሰቡ አባላት ንብረት የሆኑትን መደብሮች አንድደዋቸዋል። አነስተኛ የሸቀጥ መደብሮችን ለማቆም እድሜያቸውን ሙሉ የደከሙ በአንድ ጀንባር ድካማቸው ሁሉ ወደ አመድነት ተለውጧል። ብዙዎች ወደ ጎዳና ተዳዳሪነትና ለማኝነት ተለውጠዋል። ይህ ሁሉ ሆኖም እስካሁን ለፍርድ የቀረበ አንድም የለም። ባለፉት ጥቂት ወራት የሲዳማ አሸባሪዎች በተደጋጋሚ የመንግሥት መስሪያ ቤቶች፤ ትምህርት

« ይህ አገር የወረስነው ሳይሆን የተዋስነው ነው። » (አቶ ዮናስ ደስታ)

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ  የጠ/ሚር አብይ አህመድ            ሦስተኛው … ው መዶሻ በአቶ ዮናስ ደስታ። „ ሳቅን እብድ ነህ፤ ደስታንም፤   --- ምን ታደርጋለህ ? አልኩት። “   መጽሐፈ መክብብ ፪ ቁጥር ፪ ከሥርጉተ©ሥላሴ። Seregute©Selassie 24.04.2019 ከእመ ብዙኃን ሲዊዚሻ።                                                 የማግሥት ባለውለታ! ·        ከፍል አራት ማጠቃለያ። እንዴት ናችሁ ክብረቶቼ ደህና ናችሁ ወይ? ክፍል ሦስትን በእንዲህ ነበር የከወንኩት ኢትዮጵያ አደጋ ላይ ናት በሁሉም ዘርፍ። እና የቅንጦት ጥያቄዎችን ተግ ማድረግ ይጠይቃል። አማራጭ ሳትይዝ አማራጭ ይፍረስ፤ ይናድ እያሉ ቅድመ ሁኔታ በመፍጠር መንፈስ ከመበተን መቆጠብ ይገባል። ሰላምን ማደፍረስም የተገባ አይደለም።  አቅም ያለው ነፍስ ያለው ድርጅት ዲያስፖራ ላይ ያቋቁም። በቅኝ የማይያዝ ራሱን የቻለ ራዕይ ያለው። የሌለውን አለ እያለ ኮማን ነፍስ ይዘራል ብሎ ከሚጠብቅ። ያላበቃ፤ ያልደቀቀ ነገር የለም። ስ ል ብ ነው ያለው ሁሉ … ም። ·        ስለ ነገረ ዮናስ ጥሞና እና ጽናቱ ማጠቃለያ። የአንድ ሰው ከቦታ መነሳት ለምን ብሎ መጠዬቅ ያስፈልጋል፤ ምክንያቱም ለዛ ነፍስ ኢትዮጵያ ሁለመናዋን ገብራ ነው ያበቃችው። አብሶ ሥልጣን መበቀያ ሲሆን ደግሞ ይመራል። በተገኘው ገጠመኝ ሁሉ የቀለምህን እንጥፍጣፊ እዬፈለግህ ስተሰካካ የህብረ ብሄር እናት የሆነችው አላዛሯ ኢትዮጵያ አንክሳ ትታዬናለች። የ27 ዓመት የነፃነት ተጋድሎ ለዚህ ነበር እንዲህ የወለሌ ገባታ ሆኖ ቀረ እንጂ። ከሁሉ በላይ ቅርስ እና ውርስ ላይ ያለው