ልጥፎች

ከጁን 28, 2024 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ሰውነት ለኢትዮጵያ ተፈጥሯዋ እንጂ ባዕዷ አይደለም።

ምስል
  ሰውነት ለኢትዮጵያ ተፈጥሯዋ እንጂ ባዕዷ አይደለም።     "የቤትህ ቅናት በላኝ።" የኢትዮጵያ ፖለቲካ ከቅንነት ጋር ተዋውቆ አያውቅም።   የኢትዮጵያ ፖለቲካ ሰውኛም አይደለም። የኢትዮጵያ ፖለቲካ ተፈጥሯዊም አይደለም። የኢትዮጵያ ፖለቲካ ጭካኔን መርሁ ያደረገ ነው። ስለዚህ ዘላቂ መፍትሄ ያስፈልጋል።    ኢትዮጵያ ተፈጥሯዋ #ተፈጥሯዊነት ነው። ተፈጥሯዊነቷ ትርታዋ ነው። ኢትዮጵያን እያመሳት ያለ ፖለቲካዋ ነው። እግዚአብሄር አምላክ ተፈጥሯዋን ዕውቅና የሚሰጥ፤ አክብሮ ሊያስከብራት የሚችል መንፈስ በምድሯ ይፍጠር። አሜን።    ለእሱ የሚሳነው የለም እና። ጀርመን አንደኛውንም፤ ሁለተኛውንም የዓለም ጦርነት ተሳትፎው የጎላ ነበር። ዛሬ ግን በምድሩም በሰማዩም ሥልጣኔ አንቱ ነው። ፈጣን እና ታታሪ ህዝቧ መሪ ስላገኜ።    ጀርመን ዛሬ ከኃያሉ ጎን ተሰልፋል። ይህ የሆነው #በመሪወች #አቅም እና #ትጋት ነው። ከልዩነት አንድነትን የመረጠው ጠንካራው ህዝቧ እና የመሪወቿ #ጥበብ ለሰው ተርፎ ማደር ችለዋል። በጀርመን #ጥበብ እና #ጥበበኛ #አይታሠርም ።    ብልህ ሰው ከአለበት ተፈልጎ ልምዱን፦ ተመክሮውን እንዲያጋራ ይደረጋል። #ይሸለማል ። ዕውቅና ያገኛል። ታታሪው ህዝቡ ጀርመን ይቅደም ነው። እግር ኳስ #ጨዋታ ብቻ አይምሰላችሁ።    ታላቅ ብሄራዊ የትውልድ መገንቢያ ልዩ መንፈስ ነው ለጀርመኖች። ትርታቸው ነው።በእያንዳንዱ የተጫዋቾቻቸው ንቅናቄ አትኩሮታቸው #የድርሳን ያህል ነው። ይጥራሉ ያሳካሉ። ብርታታቸው ከጥረታቸው ጋር የተዋህደ ነው።    በሁሉም ዘርፍ ንቁ እና ብቁ። ቀልጣፋ እና ስኬታማ። ሥልጡን እና መኖርን የተጠበቡ።    ኢትዮጵያ ደግ ህዝብ ሰጥቷታል። ሁሉን ቻይ። ግን ከዘመን ዘመን ለበቂ ህክምና፤ ለበቂ መጠለያ፤ ለበ

#የተረሱት። ለምርጫ

ምስል
  #የተረሱት ። ለምርጫ ማስፈራሪያ ከምርጫው በፊት ሰበብ ተፈልጎ ቀድም ብለው የታሠሩ ምንዱባን።   "የቤትህ ቅናት በላኝ።"     እንዴት አደራችሁ? ከእኛ ይዘንባል፤ ይዳምናል። የአዬር ፀባዩ ባህሬው ወርኃ #ሚያዚያን ሆኗል። ሚያዚያ እንደልቡ ነው። መዝነቡ ግን ፀጋ ነውና እቀበለዋለሁ። ተመስግን። ምን አልባት ለገበሬወች አዝመራንካልጎዳ።   እነኝህ የምታዮዋቸው የአርቲስት ሃጫሉ ግድያን ተከትሎ ሻሸመኔ፤ አርሲ ነገሌ፤ ዝዋይ፤ ሽዋ ሮቢት #አማራወች የገነቧቸው ተቋማት፤ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት ተከታዮች #ዞግ #ሳይለይ ያደሯቾቸው ተቋማት ሲነዱ፤ በግፍ ንፁኃን በጅምላ በተዘጋጄ ኃይል ሲረሸን አዲስ አበባም ታቅዶለት ነበር። ይህን በአንድም በሌላም አድምጠናል። ዒላማ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያንን በማንደድ #ለመበቀል የታሰበ ነበር። ብጥብጡ ሲነሳም ከፍ ያለ #ቀውስ ታቅዶም ነበር።    ዕቅዱን በጥዋቱ #ያከሸፋት አዲስ አበቤ አሁንም እስር ላይ ናቸው። #ማገዶ ። ሃሳቡ #ምርጫውን #ፀጥ ባለ ሁኔታ #በፍርኃት #ጫና ማሳካት ነበር። ፈፅመውታል። ያን ጊዜ የአርቲስት ሃጫሉን ግድያ በማሳበብ ፖለቲከኞችን ግርግሩን ተጠቅመው አሰሩ።    የተዋህዶ ልጆችን በገፍ ለካቴና ሰጡ። ፖለቲከኞች ተፈተዋል፦ በዚህ ምክንያት የታሠሩት። እነዚህ ምስኪኖች ግን #ተጽዕኖ #ፈጣሪም አይደሉም። #ተዕዕኖ #ፈጣሪ #ቤተሰብም የላቸውም። #በሥም አናውቃቸውም። ከሦስት ዓመት በላይ እስር ቤት ይገኛሉ። ምን አልባት የታመሙም ሊኖሩ ይችላሉ።    ቤተሰቦቻቸው በምን ሁኔታ እንደሚገኙም አናውቅም። ጠበቃ ይኑራቸው // አይኑራቸው አይታወቅም። #አዲስ #አበባን #ከጥፋት #ክሮ የታደጓት አስተዋሽ ያጡ። ዘለግ ሲልም #የተረሱ ።   እግዚአ

ካንሰር አደገኛ በሽታ አይደለም። via Dr Gupta

ምስል
  ካንሰር አደገኛ በሽታ አይደለም።   ዶክተር ጉፕታ ማንም ሰው በቸልተኝነት ካልሆነ በስተቀር በካንሰር መሞት የለበትም ይላሉ።   (1) የመጀመሪያው እርምጃ ስኳር መውሰድ ማቆም ነው። በሰውነትዎ ውስጥ ስኳር ከሌለ የካንሰር ሕዋሳት በተፈጥሯቸው ይሞታሉ።   (2) ሁለተኛው እርምጃ የሎሚ ጭማቂ በአንድ ኩባያ የሞቀ ውሃ ውስጥ በመጨመር በየቀኑ ጠዋት ከ1-3 ወራት ከምግብ በፊት መጠጣት እና ካንሰሩ ይጠፋል። በሜሪላንድ ሜዲካል ጥናት መሰረት፣ የሞቀ የሎሚ ውሃ ከኬሞቴራፒ 1000 እጥፍ የተሻለ፣ ጠንካራ እና ደህንነቱ የተጠበቀ ነው።   (3)። ሦስተኛው እርምጃ ጠዋት እና ማታ 3 የሾርባ ማንኪያ ኦርጋኒክ የኮኮናት ዘይት መጠጣት ነው ፣ ካንሰሩ ይጠፋል።   አለማወቅ ሰበብ አይደለም። ይህንን መረጃ ከ5 ዓመታት በላይ ሳካፍል ቆይቻለሁ። በካንሰር ሰው መሞት የለበትም። via Dr Gupta

#ማመን #ከዛስ?

ምስል
  #የሙሉ ዕድሜ እስረኞች። የኢትዮጵያን ፖለቲካ #ማመን አይቻልም። #እምነተ #ቢስ ነውና። "የቤትህ ቅናት በላኝ"   የኢትዮጵያ የትግል አቅጣጫ ሥር ነቀል - ታጋሽ - አስተዋይ - ሰዋዊ -: ቀና -:ቅንም ሊሆን ይገባል። ህወሃት ኢትዮጵያን ሲቆጣጠር ፕሬስ ነፃነቱ ታወጄ። ህወሃት መሠረቱን ሲይዝ ግን ነፃ ፕሬስ #ለካቴና ተሰጠ። ህወሃት ወደ ሥልጣን ሲመጣ በፖለቲካ ድርጅቶች ህብረት ነው። ከዛ በኋላ ግንፋዊ ጉዞውን ቀጠለ። አልዘለቀም። ለነገሩ ተፈጥሮው ጭካኔ እና ክህደት ነው። ይህ እንደጣለው አለመረዳቱ ነው የሚገርመኝ።    ዛሬም በህዝብ ስቃይ ፌስታ??? የጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ ሥርዓት ሲመጣም ተፎካካሪ የፖለቲካ ድርጅቶች እኩል መብት እንዳላቸው ዓወጀ። እስር ቤቶች ወንጀልን ከመከላከል ውጪ በፖለቲከኞች፤ በፕሬስ ላይ ምንም ጭነት እንደማያመጡ ሰበኩ። የለውጥ ሐዋርያ የነበሩት    1) አቶ #ለማ መገርሳ (ዶር)፤ 2) አቶ ደመቀ መኮነን፤ 3) አቶ ገዱ አንዳርጋቸው፤ 4) #ተገዳዩ ዶር አንባቸው መኮነን።   #ከዛስ ?   ኢትዮጵያ በአገር ውስጥ መፈናቀል፤ በጦርነት፤ በሴቶች መደፈር፤ በፕሬስ አፈና፤ በተጽዕኖ ፈጣሪወች ግድያ፤ በዘረኝነት እና ጭካኔያዊ አመራር፤ በራህብም፦ በኢኮኖሚ ድቀት፤ በጀምላ እስር እና ግድያ፤ በዲፕሎማሲ የምትብጠለጠል አገር ሆነች።   የኢትዮጵያ ፖለቲከኛ ቃል #የሳሙና #አረፋ ነው። የተገባው ቃል ኪዳን ወዲያው ተኩረፍርፎ ወዲያው ይጠፋል። የኢትዮጵያ ፖለቲካ ስሜታዊ፤ ጭካኔ - ዘለቅ፤ ቂመኛ፤ በቀለኛ፤ #ፍፁም #የማይታመን ፤ ምህረት - የማያውቅ፤ ኃላፊነት እና ተጠያቂነት የማይሰማው፦ በቃሉ ፈፅሞ የማይገኝ፤ #አድመኛ ፤ ኢጎን መሠረቱ ያደረገ፦ #ሂስ ፈፅሞ የማይፈቅድ፤ ጥላቻ ገበሩ የሆነ፤ #ዕ