#ነገን መሥራት ይቻላል

 ለትውልድ እያንዳንዱ ሰከንድ ዕሴት አለው። #ዕሴቱ እንዳይባክን ትውልድ #ጊዜውን ማደራጀት ይኖርበታል። ጊዜ ማደራጀት ከተቻለ ሕይወትን በዕቅድ መምራት ይቻላል። ሕይወትን በእቅድ መምራት ከተቻለ በዛሬ ውስጥ #ነገን መሥራት ይቻላል። በነገ #መሠራት ውስጥም ከነገ ወዲያ #መሠረቱ ይጣላል። ዬትውልድ ተከታታይነት ቁምነገር የሚገነባው በራስ ውስጥ በሚሰራ የተደራጀ ተግባር ነው። በራስ ውስጥ የተደራጀ ተግባር ከኖረ ራስን #ለማድመጥ በቂ ጊዜ ይኖራል። ያ በቂ ጊዜ ሩቅ ይታሰብበታል። ታስቦም ይተገበርበታል። ያ ተግባር ሲዋህድ የማህበረሰብ ይሆናል። ሁሉም እራሱን #ያጥና እያልኩ ነው። ትውልድ የቅልቅሎሽ ድራማ አይደለምና። ሥርጉትሻ28/06/024

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም።

እህት አጊቱ ጉደታ አገር ነበረች።

አብይ ኬኛ መቅድም።