ልጥፎች

ከሴፕቴምበር 24, 2025 ልጥፎች በማሳየት ላይ

«በሞኝ ክንድ ጉድጓድ አይለካበትም።» "የውክልና ጦርነት" አይኖርም አሉ።

ምስል
  «በሞኝ ክንድ ጉድጓድ አይለካበትም።»   ብዙ ጊዜ ሃሳባቸውን ሲለዋውጡ ስለማያቸው ልብ የሚያስጥል ባይሆንም፣ አሁን ላለው የቀንዱ ውጥረት ግን ጠቃሚ ውሳኔ ነው። በትክክል ገብቷቸው ይህን አቋም አጽንተው ከቀጠሉበት " በሞኝ ክንድ ጉድጓድ አይለካበትም? ኢትዮጵያዊው ብሂል ዘመን ሰጠው ማለት እችላለሁኝ። አንድ የአገር መሪ፣ ወይንም የአንድ ንቅናቄ መሪ በዓቱን ከጦር ሜዳነት መከላከል ብልህነት ነው።   ይህ ዜና ከጸና ለኢትዮጵያ የምሥራች፣ ለግብጽ ግን መርዶ ይመስለኛል። የግብጽ የፖለቲካ ሊቃናት ኮተት እያሉ የሚድሁበት መንጠላጠያ ፍላጎታቸው አንኳሩ ኢትዮጵያን መፎካከር፣ የአፍሪካ መሪ ሆኖ ለመውጣት ማለም ነው። አባይ ምክንያታዊ የመንፈስ ማረፊያቸው ቢሆንም ፋንታዚያቸው ግን የአፍሪካ አንከር መሆን ነው። የእኔ መረዳት እንዲህ ነው። ሥርጉትሻ 2025/09/24   ዝርዝሩን BBC አማርኛው ዘግቦታል።    https://www.bbc.com/amharic/articles/c62ld9dy4v2o «የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ኢትዮጵያ እና ግብፅ በአገራቸው ውስጥ እንዲዋጉ እንደማይፈቅዱ ተናገሩ የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድ በአገራቸው በሰላም ማስከበር ላይ የሚሰማሩ የኢትዮጵያ እና የግብፅ ወታደሮች ወደ ግጭት ሊገቡ የሚችሉበት ምክንያት እንደሌለ በመግለጽ "የውክልና ጦርነት" አይኖርም አሉ።   ፐሬዝዳንቱ ከቢቢሲ ፎከስ ኦን አፍሪካ ቴሌቪዥን ጋር በነበራቸው ቃለ ምልልስ ላይ እንደተናገሩት በሁለቱ አገራት መካከል "በሶማሊያ ምድር" የሚካሄድ ጦርነት እንደማይኖር እና ሶማሊያም ይህንን እንደማትፈቅድ አሳውቀዋል።   የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድ በዚሁ ቃለ ምልልሳቸው ላይ ኢትዮጵያ እና ግብጽ በሶማሊያ ውስጥ ግ...

አብሶ በትምህርት ዘርፍ #ዛሬን #ሳያመልጥ መሻማት ነገን #ያበጃል። ዛሬ አጀንዳ ሲሆን ነገ #ያበራል። ነገ በዛሬ #የተባ ድርጊት ብቻ ነው የሚገኜው።

ምስል
  አብሶ በትምህርት ዘርፍ #ዛሬን #ሳያመልጥ መሻማት ነገን #ያበጃል ። ዛሬ አጀንዳ ሲሆን ነገ #ያበራል ። ነገ በዛሬ #የተባ ድርጊት ብቻ ነው የሚገኜው። #ምዕራፍ ፲፯   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።     #ጠብታ ።   በአገሬ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ነክ ጉዳዮች፤ ለዛውም በአማርኛ ቋንቋ ፕሮፖጋንዲስት አያስፈልገኝም። ከጋሜየ እስከ ሙሉ ዕድሜ ተዘለቀበት እኮ። የሠራሁበት እኮ ነው። በሌላ በኩል እያንዳንዱ ሰው በራሱ ህሊና የመጠቀም ሙሉ መብት አለው። በክራይ፤ በወለድ አገድ እስካላያስያዘው ድረስ። ሙሉ ዕድሜየን ነፃነቴን ለማንም ለምንም አሳልፌ ሰጥቼ አላውቅም። እኔን ሆነ ህሊናዬን አከራይቼ አላውቅም። የፈለገ አገረ ገዢ ይሁን። የፈለገ ሚሊዮኖች ይከተሉት። በሌላ በኩል ደግሞ እኔ ጎርፍ አምጥቶ ደለል የሠራብኝ ሴት አይደለሁም። ወይንም አብይዝም ሲመጣ አብሬ መጥቼ #ደራሽ ፖለቲከኛም አይደለሁም። ህሊናየንም ለማንም አከራይቼ አላውቅም።    በፊት ለፊቴ፥ ይሁን በጀርባየ የማስከትለው የሌላ አካል ወይንም ተቋም ወይንም የግለሰብ ፍላጎት እና አጀንዳም የለም። #እኔ እኔ ብቻ ነኝ። በቃ! እኔ እማስበው ከውስጤ የፈለቀ ሃሳብን ነው ሼር እማደርገው። በሌላ በኩል አንድም ቀን የእኔን ግራ ቀኝ ዩቱብ ቻናል፤ ብሎግ፤ ፌስቡክ፤ ራዲዮ ፕሮግራም ሳብስክራይብ፤ ሼር ላይክ አድርጉ ብየ አላውቅም። ወይንም #ፈንድ አድርጉልኝ፤ #ዶኔት አድርጉ ብየ ጠይቄም፤ አስቸግሬም አላውቅም። ለምን? ነፃነቴን አብዝቼ እሳሳለትአለሁኝ።   የማስበውን በነፃነት የሚያስገልጸኝ ይኽው መስመር ብቻ ነው። በሌላ በኩል የሰውን ልጅ ፈቅዶ ያድርገው እንጂ እኔ ልጫነው አይገባም የሚል ሙሉ እምነት አለኝ። ፌስቡክ ላይ ሼር እ...

"ለልጆቻችሁ የግእዝ ስም ማዉጣት ይፈልጋሉ ?"

ምስል
  ከአቶ ዋስ ያገኜሁት ትምህርት ነው። ይጠቅማል ትርጉም ማወቅ። " ማዕዶት" የሚል በጸጋየ ድህረ ገጽ አንድ መምሪያ ነበረኝ። እኔ በአማርኛ እርባታውን ተጠቅሜ ነበር ማዕዶት ያልኩት። ማዕድ የሚለውን ሥረ ቃል መነሻ አድርጌ የጥበብ ምግብ እንደማለት ነበር የተጠቀምኩት። በአማርኛ ፍሰት እኔ ተ ፊደልን ስለምወደው ሁልጊዜ ቃላትን ሳራባ ተን እጨምራለሁኝ። ሥርጉተ ወዘተ ነው ። የሆነ ሆኖ በግእዝ "መሻገሪያ" ማለት እንደሆነ ትርጉሙ ይገልፃል። አባ በጸሃ የሚባሉ የቄስ ትምህርት አስተማሪየ የቅኔም መምህር አንዱ መፃህፌ ላይ ግጥም ጽፌላቸዋለሁኝ። ትርጉሙን ዛሬ አገኜሁት "ደረሰ" ማለት ነበር ለካ።   "ለልጆቻችሁ የግእዝ ስም ማዉጣት ይፈልጋሉ ?"     "1 ማዕዶት፦መሻገሪያ ማለት ነው 2 ኖላዊ፦ጠባቂ ማለት ነው። 3 ማኅቶት፦ብርሃን ማለት ነው 4 ኂሩት፦በጎነት ማለት ነው። 5 ሜላት፦የሐር ግምጃ ማለት ነው። 6 ኅሩይ፦ምርጥ የተመረጠ ማለት ነው።ለሴት ኅሪት 7 ሮዛ፦ጽጌረዳ ማለት ነው። 8 ቀጸላ፦አክሊል ማለት ነው። 9 አስካል፦ፍሬ ማለት ነው። 10 በጽሐ፦ደረሰ ማለት ነው። 11 መሐሪ፦ይቅር ባይ ማለት ነው። 12 መንክር፦ልዩ ማለት ነው። 13 ሥሙር፦የተወደደ ማለት ነው። 14 ሐመልማል፦ለምለም ማለት ነው። 15 ነጸረ፦አየ ተመለከተ ማለት ነው። 16 ቅድስት፦ልዩ ምስጉን ማለት ነው።ቅዱስ ለወንድ ነው። 17 ይኄይስ፦ይሻላል ማለት ነው። 18 ጥዑም፦ጣፋጭ ማለት ነው 19 ግሩም፦የተፈራ ማለት ነው። 20 ተቅዋም፦መቅረዝ ማለት ነው። 21 ጸገየ፦አበበ ማለት ነው 22 ደምፀ፦ተሰማ ማለት ነው። 23 ጎሐጽባሕ፦የንጋት ኮከብ ማለት ነው። 24 ሐዋዝ፦መልካሙ ማለት ነው። 25 ሰናይ፦መልካሙ ማለት ነው።ሰናይት ለሴት ነው።...