የአብን መሥራች ጉባኤ ልዩ የምሥራች ነው - ለእኔ።
የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ መሥራች ጉባኤ ታላቅ የምሥራች ነው። ከሥርጉተ ሥላሴ ሲዊዘርላንድ 09.06.2018 (ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ።) „ሁሉ በሥላሴ ፈቃድ ተፈጥሯልና፣ ይህ ለምንድን ነው ያ ለምንድን ነው የሚል የለም።“ (መጽሐፈ ሲራክ ምዕራፍ ፴፬ ቁጥር ፳፩) ብሥራት አባተ። የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ መሥራች ጉባኤ በባህርዳር እዬተካሄደ ስለመሆኑ ዛሬ ግንቦት 09.06.2018 ከሚሊዮኖች ድምጽ ከጋዜጠኛ ሙሉጌታ ሽፈራው እና ከዘሃበሻ ደስ የሚል ዜና አሁን ተደምጧል። ይህ ትውልድ ከቶውንም ሊረሳቸው የማይችለውን የሰብዕዊ እና የሰላማዊ ትግል መብት ተሟጋቹን የፕ/ አስራት ወልደዬስን ቅዱስ መንፈስ በባዕቱ ዳግም ትንሳኤውን ያወጀ እጅግ ታሪካዊ የምሥራች ነው። አማራ ለ43 ዓመት በሥውር ህሊናው ሲመዘበርበት የነበረውን ዘመን ማክተሚያሚ ላይ ይህ መረጃ ሲመጣ ታላቅ የሰናይ ቀን ነው። አማራ አቅሙን፤ ብልህነቱን፤ ችሎታውን፤ ተመክሮውን፤ ክህሎቱን፤ ሰብዕናውን፤ በራሱ አቅም ልክ ፖለቲካውን ዕውቅና እና ተቀባይነትን አስጥቶ ትውልዱ የሚሻውን ማናቸውንም የዜግነት ሙሉ መብት በእኩልነት ለማስከበር የሚያስችል ቁመና ላይ ለመገኘት ብዙ መጣር አለበት። ሥሙን ወድጀዋለሁኝ። አማራ አገሩ ኢትዮጵያ ናት እና። ገና ውጥን ስለሆነ ተጠልፎ እንዳይወድቅ ከኦህዴድ ብልህ መሪዎች ሰፊ የሆነ ተመክሮ መውሰድ አለበት። ኦህዴድ በራሱ ላይ በ