ልጥፎች

ከኦገስት 6, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ሃይማኖት ብሄር የለውም!

ምስል
  የጅጅጋው ጥቃቱ ከብሄርሰብ ጋር መያያዝ አይገባውም። „ድሀና ግፈኛ ተገናኙ እግዚአብሄር  የሁለቱንም ዓይን ያበራል።“  መጽሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ ፳፱ ቁጥር ፲፫። ከሥርጉተ ©ሥላሴ 06.08.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። ጤና ይስጥልኝ የኔዎቹ እንዴት አመሻችሁ ዋላችሁ አደራችሁ። የጸና ደስታ የጸና ሃዘን ሁለቱም ሲያሰኛቸው በፈረቃ፤ ሲሻቸውም ደግሞ በአንድነት እዬሰላለቁን አመቱ ሊጠናቀቅ አንድ ወር ይቀረዋል። ባለፈው ዓመትም ይህን ሰሞን እስከ ፆመ ጽጌ መፍቻ ድረስ መሰሉ ፈተና ገጥሞን ነበር። የዛሬው የታቀደው የቅድስት ተዋህዶ እና የእስልማና ሃይማኖትን ምክንያት ፈልጎ አጋጭቶ አገራዊ ብጥብጥ ለማስነሳት ነው። የቅዱስ ሲኖዶስ እርቀ ሰላሙ የውስጥ እሳት የሆነበት የመቀሌው መንግሥት አቅዶ የከወነው ነው። ይህን ፍርድ ሰጪው መዳህኒዓለም ነው። ለዚህም ነው እኔ ግንቦት 7 ሆነ ኢሳት አገር ቤት መሄድ አይኖርባቸውም የምለውም ። የአብይን መንፈስ መቀበል መልካም ነገር ነው፤ ይሄው ብራናው አርፏል። ህውከት የለውም። እናግዘው ይህን መንፈስ ከተባለ ሳሄዱ ውጭ እያሉ ብዙ ተግባራትን ሊከውኑ ይችላሉ ግንቦቶች እስከ ሚዲያዎቻቸው ድረስ። ወያኔ ሃርነት ትግራይ ቂመኛ ነው። የፈለገ ይቅርታ ቢባል፤ ፍቅር ቢባል ልባችሁን አውልቃችሁ ብትሰጡ አይቀበለውም። ሌላውም እንዲሁ ነው። ይህን በሚኒ መንትዮሽ ጉባኤ አይተነዋል። ስለምን ልባችን ድፍን አድርጎ እንደ ፈጠረን ይጨንቀኛል። ሌላው ይህ እልቂት የአማራ ጥቃት ብቻ አይደለም። ሃይማኖት ዘር እና ጎሳ የለውም። ቅደስት ተዋህዶ የመላው ኢትዮጵውያን ቤት ናት። የሁሉም ዓውደ ምህርት ናት እንጂ አንድን ዞግ ወይንም ብሄር ብቻ እምታሰባስብ አይደለችም። ጥቃቱ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ነው። የ

አማራነት ሌላውን አጥቂነት ሳይሆን ራሰን ጠበቂነት ነው።

ምስል
ምን ስለሆነ?ምንስ ስለተገኘ? „ደምን ለማፍሰስ የሚሹ ሰዎች ፍጹሙን ሰው ይጠላሉ።“ መጽሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ ፳፱ ቁጥር ፲ ከሥርጉተ © ሥላሴ  06.08.2018  ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ።    ይህን የህዝብ ሙሉ የፍላጎት ድምጽ ጥሰህ እንዴት "የወጣት ብቻ" ትለላህ? ·        ጠ ብታ። የግራሞት ሰሞናት ነው። አንድ የቪዲዮ ክሊፕ አዬሁኝ „አብይ አማራን ከሁለት ከፈለው“ ይላል። ግን ቅናዊ ትህትናዊ ነው። አጀብ ነው። ምን አድርገው ነው ዶር አብይ አህመድ  አማራን ከሁለት የሚከፍሉት? የሰበኩት ኢትዮጵያዊነትን ነው። አማራ ደግሞ ሙሉ 27 ዓመት የተጨፈጨፈበት ዘሩ እንዲፈልስ የተደረገበት ዋናው አምክንዮ ይሄው ነው። ·        በመከ ራ የተወለደ የማንነት ተጋድሎ። አማራ አማራ ነኝ ያለው እኮ በሀምሌ አምስቱ አብዮ ነው። ከዛ በፊት እኮ እኔ ኢትዮጵያዊ ነኝ በማለት ነው የቀራንዮንም፤ የጎለጎታም የመከራ ጽዋ ብቻው ዕጣ ነፍሱን  ሲጨልጥ 27 ዓመት ሙሉ የኖረው። አማራ ነኝ ሲል ደግሞ አሸባሪ ነህ ተባለ።  ስለዚህ ኢትዮጵያ ሚስጢር ናት ስትባል ትናንት ያሳበዳቸው አሁን ሚኒ ጉባኤ ላይ ያሳኙን ባለተውኔቶ ሞደሬተሮች ይጨነቁበት፤ ለእኛማ የኖርንበት ማተባችን እኮ ነው። እስኪ መቼ ነው አማራ ከዛ  አፍሪካ የነፃነት ዓርማ ከሆነው አረንጓዴ ቢጫ ቀይ አርማው ውጪ ለሰከንድ መንፈሱ ወጥቶ የሚያውቀው?  አሁን አንዳንድ የውጭ አገር ሚዲያዎች አዲስ ዝግጅቶች አያለሁኝ በዛ ብሄራዊ ሰንድቅ ዓላማ ፊደሎችም ዝግጅቱም ተሽሞንሙኖ የሄዱበት ዥንጉርጉርነት ከንቱ መሆኑን አማራ መሬት ላይ በተከተታይ ለሦስት ዓመታት ስላወጀላቸው አለን እያሉ ነው። እንደ ገናም ያው መናጆ አማራ ነገ ደግሞ እንደ አብራሃሙ በ

ስለምንፈልገው ነፃነት ዝግጁነት አይነሰን።

ምስል
ዝግጁነት። „ፌዘኞች ከተማቸውን ያቃጥላሉ፤  ጠቢባን ግን ቁጣን ይመልሳሉ።“ መጸሐፈ ምሳሌ ተግሳጽ  ምዕራፍ ፳፱ ቁጥር ፰ ከሥርጉተ ©ሥላሴ 06.08.2018 ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ። ·        መቅድ መ ሃሳብ። ተወዳጇ ፆመ ፍልስቲት መጣችልን። ፆመ ፍልሰቲት ቀኗ አጭር ግን እጅግ የተመስጦ እና የሱባኤ፤ የምህላ እና የሰጊድ፤ የተደሞ እና የትሩፋት ጾም ናት። ፍልሰቲት የውስጥ ሰላም ማስፈኛ ወቅትም ናት። አማና ይህን ጊዜ፤ ታች አምና ይህን ጊዜ፤ ከዛም በፊት ይህን ጊዜ ሃይማኖታዊ በሆኑ ጉዳዮች የሱባኤ ወቅቱን ውስጣችን ጥቁር ለብሶ ነበር የተከወነው። ተስፋችን በልዑል እግዚአብሄር ብንጥልም ከቀን ወደ ቀን እዬጠነከረ በመጣው ጭካኔ ምክንያት ተስፋችን፤ እምነታችን፤ ጽናታችን የፈተኑ እጅግ አስቸጋሪ ጊዜን አሳልፈናል። እነሆ ዘንድሮ በልዑል እግዚአብሄር ቸርነት እና ፍቃድ ብጹዕን አባቶቻችን፤ ሊቃውነት ቤተክርስትያን በአኃቲ ልቦና ሆነው ሱባያቸውን የሚይዙበት የተባረከ፤ የተቀደሰ ጊዜ ላይ እንገኛለን። ተመስገን! በውስጣችን ትፍስህት፤ ተስፋ፤ ማግስትን አስበን፤ መኖራችን የፈቀድንበት ወቅት ላይ ነን። ስለሆነም የ2010 ጾመ ፍስቲት ከወትሮው በተለዬ በውልዮሽ ማዕዶተ ፍቅር፤ በውልዮሽ ማዕዶተ መተሳሰብ፤ በወልዮሽ ማዕዶት መከባባር ፍለስቲት በጥልቅ የተመስጦ መንፈስ አምሮባት ትከወናለች ማለት ነው።  ተመስገን! ሳይሽ እወላለሁ ከልቤ አስቀምጬ ሳይሽም አድራለሁ አቅፍ አንተርሼ አወሳሳሻለሁ አድርሽኝ ለብሼ አንቺን እዬሳሳሁ ጀግንነት ወርሼ እንደ ወጣሁ አልቀር አይቀር እንደ መሼ፤ „አድርሽኝ“ ግጥም ለህትምት የበቃ ነው፤ ሁልጊዜም በጸጋዬ ራዲዮ ላይ እንደ ድርሳን የመግቢያ መዝሙሬ ነ