ልጥፎች

ዝም አትበሉ መንገርም ማናገረም መልካም ነው።

ምስል
ግዙፉ የግንቦት 7 ፈተና። „ደሴቶች ሆይ በፊት ዝም በሉ አህዛብም ሃይላችውን ያድሱ፤ ይቅረቡም በዚያን ጊዜ ይናገሩ፤ ለፍርድ በአንድነት እንቅረብ“ ትንቢተ ኢሳያስ ምዕራፍ ፵፩ ቁጥር ፩ ከሥርጉተ©ሥላሴ  05.08.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። ·       መራረነት ጣፋጭነትም የእግዜሩ ሰውኛ ናቸው። የዚህ ጹሑፍ ጭብጥ የሚመራቸው ይኖራሉ። ያው ሥርጉተ ሥላሴ እንደምትማራቸው ዓይነት። ግን ዘመኑ መራራን ማድመጥ አትራፊ ስለመሆኑ እዬታዬ ነው። መራራውን መናቅ ደግሞ የውድቀት መጀመሪያ ስለመሆኑም ዘመኑ ተመሰጠረበት። ከመራራዎቹ አምክንዮች ነው ዛሬ ላይ ትርፍ እዬተዛቁ የሚገኙት። ከ66 አብዮት ማግስት ነገረ አማራ በጥርስ የተያዘ ግን በመናጆነት የተቸነከረ ጉዳይ ነበር። የመፍትሄው ቁልፍ ግን ከነገረ አማራ ላይ የተነሳ መንፈስ ብቻ ነበር። ማለት አማራነት መራራነት ነበር ግን በራሱ አቅም ውስጥ ጎልቶ እንዳይወጣ ቁልጭ ያለ መድሎ ነበር። አሁንም አለ ትሉ ይሆናል ጊዜው ልጅ ነው እና የአብዩን መንፈስ በዚህ መንቀስ ብዕሬ አትደፍረውም። ላያቸውም የምፈቅዳቸው የጊዜ ሰንጠረዦች አሉና ...  ነበር ስል ግን አሁን የለም ለማለት አይደለም። አልተጀመረም ቀድሞ ነገር። ነገረ አማራ በፖሊሰ ደረጃ ነው ጭቆናውም፤ ግለቱም። ስለዚህ ተንስኤው የፖሊሲው መወገድ ብቻ ሳይሆን እጭ የሰሩ ጸረ አማራ እሳቤዎች ጊዜ ብቻ ነው ነቅሎ የሚጥላቸው። ዛሬ እንኳን በ እኛ አቅም ለተገኘ መባቻ የሚታዬውም፤ የመደመጠውም ድፍረት ማጣቱም እዬታዬነው።  ይህን መሰረት ለማስያዝ በራስ ውስጥ የበቀለ አቅምን በመገንባት ብቻ የሚገኝ ነው። ይህም መራራ ጉዞ ነው። አሁንም አማራነት መራራነት ነው። የትኛውም አካል  ለድል ካበቃ ወይንም መሬት የረገ

አለማወቅን በዕውቀት መቀበል መቻል።

ምስል
ጥሞና ስለህሊና። „ውኆችን በእፍኙ የሰፈረ ሰማይንም በስንዝር የለካ፣ የምድርንም አፈረ በመስፈሪያ ሰብስቦ የያዘ፤  ተራሮችን በሚዛን ኮረብቶችንም በሚዛኖች  የመዘነ ማን ነው?“ ትንቢተ ኢሳያስ ምዕራፍ ፵ ቁጥር ፲፪ ከሥርጉተ © ሥላሴ።  05.08.2018 ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ።  ·       መ ቅድመ ሃሳብ። የኔዎቹ ቅኖቹ ውዶቹ እንዴት ናችሁ? በዬወቅቱ አዳዲስ ፓርቲዎች፤ ውህደቶች፤ ህብረቶች ይፈጠራሉ። አዲስ ሁኔታ በተፈጠረ ቁጥር በመገላበጥ ወይንም በመመሰጥ አዳዲስ ሁነቶችን የተከተሉ በዬዘመኑ አዳዲስ ሊሂቃን፤ ታታሪዎች፤ ጋዜጠኞች፤ ተንተናኞች ይወጣሉ። አብሶ ፓለቲካ ድርጅት መሠራቾች ሊሂቃን ከወጡ በኋዋላ በመቀደም ይሁን በመሰበር የጀመሩትን ሳይጨርሱ ሲከሽፍባቸው በሌላ ሁኔታ ደግሞ አዲስ ዓላማ በአዲስ ሥያሜ ሌላ ውጥን ይዘው ይነሳሉ፤ ይህ የማያቋራጥ በዙር ተመለስ የታዬ ጉዳይ ነው ነገም ቀጣይ ነው። አብን እማዬውም ከዚህ አንጻር ነው። ከታጋድሎው መንፈስ ጋር አብሮ እንኳን መፈጠር አልተቻለውም አብን። እጅግ ዘግይቶ ለዛውም አስቸኳይ ጊኤዜ አዋጅን ተንትርሶ እና አዲስ ጠ/ ሚር መንፈስ ሲፈጠር ነው ከች ያለው። የነገ ቀጣይነት  ለሚለው ዋቢ የሚሆነው የድርጅቱ አመሰራረት ሁኔታ ወሳኝ ነው። ሞረሽ በቀደመው ፍልስፍና ቀጥሎ ቢሆን ኖሮ ዘላቂ ስኬቱ አንቱ በሆነ ነበር። ምክንያቱም አመሠራረቱ መርህ እንጂ ወጀብ ስላልነበር። ነገር ግን እሱም አንዛላለጠው እና ወደ ፖለቲካ ድርጅትነት የተለወጠበት አሰገዳጅ ሁኔታ የአማራ ተጋድሎ መምጣት ነበር። የተጋድሎውን መንፈስ ሳያጣጥም ነበር በሽሚያ ወደ ፖለቲካ ድርጅትነት የተለወጠው።  ዘላቂ ዓላማ ቢኖር ቀድሞውንም ሞረሽን በተረጋጋ ሁኔታ የፈጠረው መንፈስ

የወግ ገብታ ... ለመንፈስ ዝና።

ምስል
ካለ ቀጠሮ „ሣሩ ይደርቃል፤ አበባውም ይረግፋል፤ የአምላካችን ቃል ግን ለዘላዓለም ጸንታ ትኖራለች።“ (ትንቢተ ኢሳያስ ምዕራፍ ፵ ቁጥር ፩) ከሥርጉተ©ሥላሴ 05.08.2018  (ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ።) ·       ማካሄጃ።    የኔዎቹ ክብረቶቼ እንዴት ናቸሁ? ያው ነው ይህ ዘመን እንዲህ ነው ኃዘን ተፍሰኃ፤ ትናንት የሰላም ወዳዱ የኢትዮጵያ ህዝብ የትፍስህት ቀን ነበር፤ የክርስትና እና የእስልምና ዕምነት ሊቃውንታት ቤታችን፤ ማዕዳችን መነሻችን መሰረታች ሲሉ በአሃቲ ቅን ልቦና ቅድስት ኦርቶዶክስ ተዋህዶን ወስጣቸው አድርገዋታል፤ ዲያቢሎስም ቅስሙ ተሰብሯል፤ የ27 ዓመቱ የወያኔ ሃርነት የፖሊሲ ቅስም እንኩት ብሎ እንጦርጦስ ተልኳል። ተመስገን! የቅድስት ቤተክርስትያናችን ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ማህበረ ምዕምኑ በሙሉ የሌሎቹን እምነቶችን አቦን በልባቸው ፍሬ ነገር መጸሐፍ የጻፉበት የውል የኪዳን ብፅዕት ዕለት ነበር። እንኳን ደሰል አለን! በሌላ በኩል የሁለቱ ብፁዓን አባቶች የክብር አጠራር ወጥ አልነበረም። ዝበት ነበረው። ይሄ በቤተክርስትያን ወግ እና ሥርዓት የተገባው ትኩረት ሊሰጠው ይገባል። ሥርዓተ አልበኝነትን አይቻለሁኝ። እንደ አባት አደሩ ሊሆን ይገባል። ቤተክርስትያናችን ለሁለመናዋ ሥርዓተ ህግጋት ቅደምት ተከተል አላት። ከማንም ከምንም ችሮታ አትጠይቅም። አባ ዝምታ ቅደስናቸው እጅግ የጠለቀ በመሆኑ ዋጋው የሚወራረደው በመንፈስ ቅዱስ ሃይል ነው። መበጠስም ያመጣል።    በሌላ በኩል ደግሞ ልባችን የተሰበረበት የፍቅር ከተማዋ ደግሞ ቃጠሎ ነዲድ፤ ይህም አልበቃ ብሎ የወገኖቻችን  ተስፋ ደግሞ እንደ መባጃው ስደት ወደ ጁቡቲ … ሆኗል። የተሰጠን ይሄው ነው፤ ወይ ተረግማናል ወይ ረግማናል ሌላውን ያለ አግባብ።

የልጆች የህይወት ዳገታዊ ግማድ። እስጨናቂው ዕጣም።

ምስል
ወላጃዊ ግዴታን በመወጣት እረገድ የትውልዱ ዕጣ መለጣ እንዳይሆን ቢታሰብበት መልካም ነው። አምላኬ አምላኬ ለምን ተውኸኝ? እኔን ከማዳን ከጩኸት ቃል ሩቅ ነህ? (መዝሙር ምዕራፍ ፳፩ ቁጥር ፩) ከሥርጉተ © ሥላሴ 04.08.2018 (ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ) ·        የመጓጓዣ ሃሳብ። ይህ ርዕሰ ጉዳዬ ዛሬ ባለሁበት ዕድሜዬ ያሳብኩት አልነበረም። ይህን ገና ታዳጊ ወጣት እዬለሁኝ ከውስጤ የነበረ አብሮኝ ያደገ ደሜ ነው። አብሮኝ እንዲያድግ የሆነበት ምክንያትም እብዬ እና አቨይ ሲለያዬ የማወቀው ታሪክ ስላልነበረኝ አድጌ ነፍስ ሳውቅ እኔ ከእናቴ ጋር መሆኔን ሳረጋግጥ በራሱ ጊዜ በመንፈሴ የተጸነሰ ይመስለኛል። መራራ የደም ቅምረት ላረሳው ላይረሳኝ ተዋደን በአንድ ማዕድ አብረን የኖርን ግማድ። ከዚህ በተጨማሪ ከወላጆቻቸው ጋር በጋራ ከሚያድጉት ይልቅ እንደ እኔ ከእናታቸው ጋር የሚያድጉት ዕድል ያሸለበችባቸው እጅግ በርካታ ህፃናት የመንፈስ ምሾም ህሊናዬን እንዳይተኛ አድርጎ ኮትኩቶ ስላሳደገውም ጭምር ነው። ከአደግኩ በኋዋላ እንደተረዳሁት ማግባትም መፍታትም ገብያ ሄዶ እቃ እንደ መግዛት እጅግ ቀላሉ የህይወት ክፍለ አካል መሆኑንም ተገንዝቢያለሁኝ። በህይወቴ ከሚያሥፈሩኝ ነገሮች ትልቁ ትዳር ሆኖ በልቤ ጽላት የተከተበውም በዚኸው የመከራ ጠመኔ መሆኑ ዛሬ ዛሬ ይረዳኛል። ላም ጣም ለሌለው ሕይወት ስለምን የሰው ልጅ ጉልቻን አህዱ ይለዋል?  አሳዛኙ ነገር በእኔ አልበቃ ብሎ እህቶቼም በዚህ ውስጥ ኑሯቸውን መወሰናቸው ዛሬ ላይ ውስጤን ያርመጠምጠዋል። ከማህበረሰቡም፤ ከቤተሰብም ያዬነው የትዳር ናሙና ባለመኖሩ ታላቁን እዮራዊ ጸጋ ሸሽተነው እንድንኖር ተገደናል።  በዚህ የውስጥ ቋያ ውስጥ እንግዲህ ብዙ ማህበርተኞች