ልጥፎች

ከጁላይ 6, 2023 ልጥፎች በማሳየት ላይ

Die Gründe für den Ausschluss der Amhara von der politischen Macht.

ምስል
Die Gründe für den Ausschluss der Amhara von der politischen Macht. • Es sollte sein, Strategische Ausrichtung des Kampfes um Identität und Existenz der Amhara.     können Sie Anhängerführer? Also lass mich Dort anfangen. O.K. Haben Sie schon einmal eine Leiche stehen sehen? Lassen Sie mich Ihnen ein wenig erzählen .... • Nicht lebendig. (1) Das erste Foto, das Sie sehen, zeigt einen 27-jährigen von Amhara wie Krebspatienten. (2) Das zweite Foto, das Sie sehen, zeigt 4 Jahren Unwetter. (3) Das Foto Nummer eins sind Pro -TPLF. Nicht alle waren Amhara. Aber Sie waren Amhara Region Führer oder Verwaltungen. Die Fotos Nummer zwei stammen aus der OLF- Ära. Ihre Generation: Ihre Entwicklung, Ihre Arbeit Ort kann in der Region Amhara liegen. Sie sind fast wie Metzgerei, der die Menschen von Amhara zu getötet. (4) Nummer eins oder Nummer zwei die meisten von ihnen hatten während der TPLF-Ära in verschiedenen Positionen zusammengearbeitet. Sie sind auch wahre Freunde. Sie waren also

ኢትዮጵያን የሚመራ የአማራ #ጠቅላይ #ሚር ይናፍቀኛል።

ምስል
ኢትዮጵያን የሚመራ የአማራ #ጠቅላይ #ሚር ይናፍቀኛል።     "የሰው ልብ መንገድን ያዘጋጃል እግዚአብሔር ግን አካሄዱን ያቃናለታል።" (ምሳሌ ፲፮ ቁ ፱) የአማራ ልጅ ኢትዮጵያን የሚመራ ጠቅላይ ሚር በዘመኔ ይናፍቀኛል። አብዝቶ። እኔ ብቻ ሳይሆን ዓለምም ሊናፍቃት ይገባል። ልዕልት ፕላኔታችን እዮራዊቷን ኢትዮጵያን ማዬት ከናፈቃት ኢትዮጵያ የአማራ ጠቅላይ ሚር፣ የውጭ ጉዳይ ሚር፣ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ይኖራት ዘንድ ትትጋ። የአማራ መንፈስ የበታችነት ስሜት ድርሽ ብሎበት ስለማያውቅ የሰውን ልጅ የእግዜአብሔርን ፍጥረት ገድሎ መርካትን አይመኜውም። ነፃ ነኝ ብሎ ስለሚያምንም የነፃ አውጪ ቅልቋንቁር፣ እንቶፈንቶ፣ ቀጨር መጨሬ ሲደርት ውሎ አያድርም። ለአገር መሪነት ሙሉ በራስ የመተማመን መንፈስ ይጠይቃል። የበታችነት ስሜት ድዌ ነው። የአምሮ ህመም። ይህ ህመም ፀረ ተፈጥሮ፣ ፀረ የሰው ልጅ፣ ፀረ ስልጣኔ ነው። ዛሬ ዓለማችን በደረሰበት ድንቅ ስልጣኔ ልክ ለመጓዝ በሙሉ ሰዋዊ፣ ተፈጥሯዊ አቅም እና አቋም መንቀሳቀስ ይጠይቃል። የሰው ደም ገድሎ የሚጠጣ፣ ገድሎ ጠያፍ ከሞራል የወረደ ተግባር የሚፈፅም፣ ገድሎ ከተማ እሬሳውን ለኤግዚቢት የሚያቀብር ዲያቢሎሳዊነት ነው። በቀን በማይካድራ ከ600 በላይ፣ በቀን በወለጋ ከ2000 በላይ የሰው ልጅ እንዲህ የሚታረድባት ምድር ኢትዮጵያ ብቻ ናት። ለ50 ዓመት የአማራ ሊቀ- ሊቃውንታት ቁልፍ ከሆነው የአገር የመሪነት ቦታ ተገለዋል። የአማራን ተፈጥሯዊነት ውስጣቸው ያደረጉ አንቱ የአገር ልጆችም የሌላ ብሄረሰብ አባላት እንዲሁ ፊት ተነስተዋል። ስለዚህም ነው ኢትዮጵያ በ3000 ሺህ ዘመኗ የገነባችው ቅርስ ውርሷ፣ መንፈሳዊ አንቱታዋ፣ ሰማያዊ ሽልማቷ ጋር በተቃርኖ የቆሙ አሰሮች እዚህ ያደረሷት። ኢትዮጵያ የ

ፍትኃት እንዴት? ፍትኃት በማን? ፍትኃት ለማን? ዕለተ ሰኞ ማዕዶተ ጠባቂ

ምስል
ፍትኃት እንዴት? ፍትኃት በማን? ፍትኃት ለማን?     ዕለተ ሰኞ ማዕዶተ ጠባቂ በከበቡሽ የቁራሽ እንጀራ ብራና በቢሆነኝ የተብራራ ብራ በሰብለ ሕይወት አዝመራ ለራህብ የሚራራ። „የሰው ልብ መንግድ ያዘጋጃል፤ እግዚአብሔር ግን አካሄዱን ያቃናለታል“ (ምሳሌ 16 ቁጥር 9) • መቅድም። ውድ ቤተሰቦቼ እንዴት ሰነበታችሁልኝ? ደህና ናችሁ ወይ? ናፍቃችሁኛል!!! እኔ አምላኬ ክብሩ ይስፋ ደህና ነኝ። አሁን ደግሞ በጋ ነው። በጋ ነፍሴ ነው። ይቀለኛል። መንፈሴ ፏ ፍንትው ይላል። ይፈታታል ሁለመናው። በጋ ቢለብሱትም፤ ቢመገቡትም አይዋ በጋን እቅፍ እድርገው ቢሞጨሙጩትም፤ አሽኮኮ ቢያደርጉትም በጋ ጠሐይ ነው። ብርኃን። እና ሥርጉትሻ እና በጋዋ በመልካም ጤንነት ላይ ናቸው። ደህና ነኝ። „አድርገህልኛል እና አመሰግንኃለሁ“ • ምስጋና። (1) ጹሑፌን ያነበባችሁ፤ የተቻችሁ፤ ሼር ያደረጋችሁ የኔወቹ የእኛነት ውስጦቹ ልስልስ ያለ፤ ዘንጠፍጠፈ ያለ ሞንሟና ምስገናዬ በያላችሁበት ይድረስልኝ። አሜን። ኑሩልኝ ለእኔም ለቅኒትም ኢትዮጵያም። (2) የት ጠፋሽ? ደህና ነሽ ወይ ብላችሁ አክብራችሁ ከህሊናችሁ ሆናችሁ ስለደህንነቴ አበክራችሁ የጠዬቃችሁኝ ቤተሰቦቼ ውስጤን የምገልጽበት ቃል የለኝም። እናንተ ሰው ወዳጆች ወገኖቼ ሆይ! የእኔ ድንግል በያላችሁበት ጥላ ከለላ ትሁንልኝ። አጤ ፌስቡክ እናንተን የመሰለ አሳቢ፤ አዛኝ፤ ጠያቂ፤ አጽናኝ፤ አይዞሽ ባይ ስለሰጠኝም አክብሮታዊ ምስጋናዬን አቀርብለታለሁኝ። ፌስቡኬኛ ሳልሆን ያቃጣልኩት፤ ያባካንኩት ጊዜ እጅግ ይቆረቁረኛል። እንዲህ አይነት ወገን የሚገኝበት የአብሮነት አውድነት ፍጽምናው የልዕልና ነውና። ተመስገን። • ለምን ጠፋሁኝ? የጠፋሁት ምክንያታዊ ነበር። ከመጋቢት 18/2010 ጀምሮ እሰከ ሐምሌ 19/2010 ድርስ ምዕራፍ አንድ ነበር።

06/072019 ሌኮ አብይ አህመድን ለመደገፍ ትንፋሽ ያጥረኛል። አይ! ይድረስ ለገራገሩ ጋዜጠኛ አበበ በለው። አሜሪካ።

ምስል
  ሌኮ አብይ አህመድን ለመደገፍ ትንፋሽ ያጥረኛል። አይ! ይድረስ ለገራገሩ ጋዜጠኛ አበበ በለው። አሜሪካ።       መቅድም። ትንፋሼን ሳስበው መውቲ ይሆናል ዶር አብይ አህመድ እንደግፈው የሚል አሰናካይ ሞቶ ብቅ ሲል። እኔ በተፈጥሮዬ የተስፋ አክቲቢስት ነኝ። ከእናቴ የወረስኩት ቅንነት በተስፋ፣ ከአባቴ የወረስኩት ብዙ አለመናገር ጭምትነት በቤት ውስጥ መለያዬ ናቸው። ተስፋ ሥሙንም እወደዋለሁ። እራሱ ተስፋ የሚባል ሥም በህልሜ ሳይ ብሥራት በዕለት ኑሮዬ ይገጥመኛል። በሥነ- ፁሁፍ ሥራዎቼ ሁሉ ተስፋ ማጣፈጫዬ ነው። የመጀመሪያው ለአዋቂዎች የፃፍኩት የሥነ - ግጥም መፀሀፌም ተስፋ ነው ዕርዕሱ። ስለዚህ ተስፋ ይዤ መጥቻለሁ ለሚል የተስፋ አቀንቃኝ የህሊናዬ አውራ በር ክፍት ነው። በዚህ ላይ አዎንታዊ እና ቅንነቴ ሲታከልበት አቅሜን በድንግልና እገብር ዘንድ ሞተሬ ነው። ስለሆነም በአባልነት፣ በደጋፊነት ተመዝግቤ የፎርሙላ ታጋይ መሆንን ባልሻም ለትውልዱ የተስፋ መንገድ ይሆናል ላልኩት ተቋም፣ ግለሰብ የበኩሌን ድርሻ አበርክቻለሁ። ያባከንኩትም ጊዜ የለም። ያ ተስፋ ያደረኩበት ግለሰብ ይሁን ድርጅት ተስፋውን ሲያወይብ፣ ሲያጠነዝል፣ መንገድ ሲስት በእኔ ዕይታ ከሊቅ እስከ ደቂቅ ይሞገታል። ርህራሄ የለም። የጋዜጠኛ አበበ በለው የፌስ ቡክ ጉባኤ ዬሁለት ቀን ውሎዬ። አዲስ ድምፅ ራዲዮ ግንድ ሚዲያ ነው። ስለዚህም በቀደመው ጊዜም ሆነ ዛሬ ውይይት ሲኖረው ጎራ እላለሁ። ዛሬም እንዲሁ። ፌስቡኩን ግን በመደበኛ ሁለት ቀን ብቻ ተሳተፍኩኝ። አንዱ የአብን ግሎባል ኮንፈረንስ እና ፈንድራይዚንግ ጉባኤ ሲመራ ሙሉውን አዳመጥኩት። ጥሩ ጊዜም ነበር። ሁለተኛው ትናንት ነበር። ግሎባል የአማራ ንቅናቄ እንፍጠር የሚል ነበር። በተለይ አማራነትን በሚመለከት እራሱንም አመክንዮዊ መንፈሱንም