ልጥፎች

ከኦክቶበር 25, 2025 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ኢትዮጵያ የገነፈለ ሁሉ #ፍላት ማጠራቀሚያ በርሚል አይደለችም። ሁልጊዜም "ማህረቤን ያያችሁ" ሰለቸን። ገለማን!

ምስል
  ኢትዮጵያ የገነፈለ ሁሉ #ፍላት ማጠራቀሚያ በርሚል አይደለችም። ሁልጊዜም "ማህረቤን ያያችሁ" ሰለቸን። ገለማን!   "አቤቱ ንጹህ ልቦና ፍጠርልኝ።" አሜን።        #ምዕራፍ ፲፯   #ጠብታ ።   የኢትዮጵያን ልኳን በልኳ ልክ መጠኖ መነሳት ይገባል። ለኢትዮጵያ የክት እና የዘወትር፤ የእዳሪ እና የቤት፤ ምርጥ ዘር እና አልባሌ፤ ዓይነታ እና አሰርውሃ የሚባል ጉዳይ የለም። የዜግነት እርቦ እና ሲሶ የለውምና። ሺ ሚሊዮን ጊዜ ይመስጠር፤ ይከደን የሃቅ አቅም ይንደዋል። ሁልጊዜ ልበጣ በስልቃ #ቃ ያለ ጉዞ ነውና።    #ኢትዮጵያ ለከበደችው ስኬቱ አይደለም ተሸፍኖ፤ ገሃድ ሆኖም ጋዳ ነው፤ ገድጋዳ - ገዳዳም።   ሰሞኑን የልጅ ሞገስ ሚዲያ እንደ ነገረን፥ ሰነዱንም አንብቦልናል፤ አሜሪካ ላይ የተቋቋመው ልክ ግንቦት 7 "አገር ማዳን" በሚል ለዛውም ግለሰቦችን ሳይሆን ግንቦቲዝም ተቋማትን ነበር ያሰባሰበው። ያው በአሰልቺው ድግግሞሽ "ኢትዮጵያን ማዳን" በሚል እራሱን #የፈራ ፤ እራሱን የሸሸ ቡድን "አገርን ስለማዳን" ቅርንጫፋን አውሮፓ አምስተርዳም ላይ እንደ ፈጠረ ዜናውን ነግሮናል።    ልጅ ሞገስ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ላይ በትጋት እየተሳተፈ፤ አውሮፓ ተቀምጦ ስለምን እንዳላከሉት አላውቅም። የሆነ ሆኖ በግልጽ ቀርቦ ቀጥተኛ ፍላጎትን፤ ዓላማ እና ግብን ማሳወቅ የቲሙ መብት ሳይሆን ግዴታው ነው።    እነኝህ ክንብንብ ያሰኛቸው እነማን ናቸው??? ኢትዮጵያ እኮ ሉዓላዊ የተከበረች አገር ናት። በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ዕውቅና ላላት አገር፤ በገሃድ ላለች፤ ዓለም በብዙ ሁነቶች ለሚያውቃት ቀደምት አገር በስውር ቲም ትንሳኤሽን እናመጣለን #ጠብቂኝ የገ...

#ወፍሽ።

  #ወፍሽ ። ምዕራፍ ፲፯ "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን። ቀንሽ ራሄል … እንደ እኔው ሲዋልል ጥንካሬሽ ቢያባብል አሳሩ ግን #ድንብልብል ። የመከፋት ተራራ ዝልብልብ የሂደት ጉዞ ጉስቁልቁል። ልጄ ልብስ የለው መንገድ አዳሪ ዋስትና ያጣ መንገድ ላይ ቀሪ። ሞፈር ቀንበሩ ዝናብ ጠባቂ ምርተ - ውጤቱ ያልሆነ በቂ፤ #ጀንዴ የሌለው #ተስፋን ናፋቂ #ገሳ ለባሹ ለራብ ተጠቂ። ድሆኖው ባዶ ሲሳይ የነሳው ተምቹ ትንኙ ፋታ ያሳጣው፤ ጥማቱ #ጠኔው የሚነስተው በሽታ ዱላው የከተከተው። እልፈተ ቢሱ ያነ……… #ገበሬ ራዕዩን ሁሉ በላበት አውሬ። ላዋይሽ ራሄል እስኪ ነይ እባክሽ እናቴ አንድ በይ። ለምዕተ ዓመታት በአንድ #ከፈን አቶ #ማለፍን በመለመን፤ እህህ ሆነው የእሱ ዝግን የበሬው ጌታ ፍሬዘር። #የእናት አገር ምሬት። #ህዳር 3 ቀን 2001 ዓ.ም ሲዊዘርላንድ ሄርሽን ሆቴል። መክሊት የአዋቂወች የግጥም መድብል ከገጽ 98 -99 ለህትምት የበቃ። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 23/10/2025 ጊዜ ራዲዮሎጂ ነው።

ዘመንን ያናገረ ድንቅ ሰብዕና #ሐዋርያ ነው፤ #ቅኔበቃናየቀና። የሰዋዊነት ካፒቴንም ነው ልክ እንደ ክቡር (ዶር)ተቀዳሚ ሙፍቲ ሃጂ ዑመር ኢድሪስ።

ምስል
  ዘመንን ያናገረ ድንቅ ሰብዕና #ሐዋርያ ነው፤ #ቅኔበቃናየቀና ። የሰዋዊነት ካፒቴንም ነው ልክ እንደ ክቡር (ዶር)ተቀዳሚ ሙፍቲ ሃጂ ዑመር ኢድሪስ።   አቤቱ ኢትዮጵያዊው #NBC ይቅርታ ጠይቅ። መራራ ስንብት የሙዚቃ ድግስን ስለሚጸየፍ።    "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።       #ምዕራፍ ፲፯   ጤና ይስጥልኝ ቤተ ቅንነት? እንደምን ሰነበታችሁ? እኔ አምላኬ ክብሩ ይስፋ ደህና ነኝ።   ሰሞኑን #ተግ ብዬ ነበር። ምክንያቴ ኢትዮጵያ የውስጧን #ቅኔበቃናየቀናውን ልጇን ሞት ስለወሰደባት ነበር። የሆነ ሆኖ በኢትዮጵያ ህዝብ የእኛ ሃዘን ብሎ የተቀበለበት ዕውነት የእናቱን የልዕልት ኢትዮጵያ ኦርጋኒክ ተፈጥሮን ያነበበ፤ የተረጎመ፤ ያመሳጠረ ክስተት ነበር።   የዘመኑ የኢትዮጵያ ልጆች በብሄራዊ ሰንደቅ፤ በታሪክ፤ በብሄራዊ መዝሙር፤ በዞግ፤ በወሰን፤ በሃይማኖት፤ ከዚህም ባለፈ በቀጨር መጨሬው የነበረው ጉጉስ #በአደቧ ፤ #በአቅሏ ፤ #በዋርካዋ ዋርካ የሚለውን ትምህርተ ጥቅስ ያላስገባሁት በጽኑ መታመማቸውን ስሰማ እራሴው የፃፍኩት ኃይለ ቃል ስለሆነ ነው። የሆነ ሆኖ የኢትዮጵያ አደብ፤ የኢትዮጵያ አቅልን በሥጋ መለየት በሚመለከት ሃዘኑ እኩል ስለሆነ መጽናናቱን ለሁላችን ይስጠን ፈጣሪያችን // አላሃችን። አሜን። የኢትዮጵያም የምር ሃዘኗ ነው እና እናት ዓለም ሆዴ እግዚአብሄር ያጽናሽ። አሜን።   አንድ መንግሥታዊ ሥርዓት በሚወስዳቸው ማናቸውም እርምጃወች ቀድሞ የጨመተውን ማህረሰብ ዕይታ ማጥናት ይገባዋል። ሪሰርች ሊሠራ ይገባዋል። ውድቀትን ስለሚያመጣ። የክቡር ተቀዳሚ ሙፍቲ ሃጂ (ዶር) ከሃላፊነታቸው መገለል ወይንም የተገለሉበት ሂደት በምን ያህል ልክ ኢትዮጵያውያንን...