ልጥፎች

ከሴፕቴምበር 17, 2023 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ልጆቼ መፅሀፉን ቀደው ወረቀቱን በሉት. . .ሁለቱም ድል ባለ ሰርግ ተዳሩ! ማንም ካላየ አይገምትም #ethiopia...

ምስል
ይህችን የዘመን ቅኔ እባካችሁ አዳምጧት። ከአውስትራልያ ሄዳ እናትነትን በተግባር እንደምን እንዳስጌጠችው፤ ጋዜጠኝነትን እንደምን ምስባክ እንዳደረገችው፤ ሴትነትን እንደምን እንዳነፀችው በአስተውሎት መርምሩት። ኢትዮጵያ እናታችን ጎደሎዋ ብዙ ነው። ቀዳዳዋ ወዘተረፈ ነው። እንደ ድንግል ዳሳሽ ያገኙት ወንድሞቻችን ፈዋሽ እናት ሰጣቸው ፈጣሪ አላህ። ተመስገን። የእኔ ክብሮች ሰንበትን ለተፈጥሯዊነት አውለን ያለችነን እንለግስ ዘንድ ዝቅ ብዬ እለምናችኋለሁኝ። ዬባንክ ቁጥሩ 1000453519094 ነው። ለበረከት እሽቅድድም፤ ለመልካምነት ትጋት ይኑር። ፈጣሪ ይርዳን። ብሩካን ያወጋሉ። ይህ የመልካምነት ሊቀ ትጉኃን ወንድማችንም የሰጠው ነው። ሽልማታችንም ነው። እሷም ቅድስታችን። ይባረኩ። አሜን። • https://www.youtube.com/watch?v=Wl3XM6lkoDc ልጆቼ መፅሀፉን ቀደው ወረቀቱን በሉት. . .ሁለቱም ድል ባለ ሰርግ ተዳሩ! ማንም ካላየ አይገምትም #ethiopia #new #adiction #wedding • 1000453519094 ግን እንዴት ነን? አይዞን። ያልፋል። ኑሩልኝ። ደህና ዋሉ። ደህና እደሩልኝ። ሼር በማድረግ አነሰ አደገ ሳትሉ የምትችሉትን አድርጉላት። አይዞሽም ስጦታ ነው። ተባዕቶች ውጪ የምትኖሩ ልብሶችን፤ የህክምና ባለሙያወች መዳህኒቶችን፤ ስትችሉ በኦን ላይንም በነፃ የትምህርት የቴራፒ አገልግሎት ብትሰጡቸው ትባረካላችሁ። በፋይናንስ የምትችሉም እንዲሁ፤ በሚዲያም በማስተዋወቅ መርዳት ኢትዮጵያን የሚገልጽ ገፀ በረከት ይሆናል። መልካም ማሰብ በራሱ መልካምነት ነው። መታደል በጉነት ነው። ድንቂት ድንቅነቷ ምንጯ ከአበው እና እመው መንጭቶ ይህን አሳካች። ለማግሥት ባለ አሻራ ሆነች። አሻራችን እናሳድገው። እግዚአብሄር ይስጥልኝ። አሜን። ሥርጉትሻ