ልጥፎች

ከሴፕቴምበር 18, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ነገ አምጦ እንዲመጣ ሴረኞች ተግተዋል።

ምስል
ከበደ ነገ እያማጠ ነው። „እኔ ግን በምሕረትህ ብዛት ወደ ቤትህ እንተ እግባለሁኝ።  በመፍራት ወደ ቅድስናህ መቅደስ እሰግዳለሁ።“ መዝሙር ፭ ቁጥር፯ ከሥርጉተ©ሥላሴ 18.09.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ በአንቦ ሌላ የከበደ ዜና ተደመጠ። እርግጥ ነው የተጎዳ ወገን እንደሌለ ዘገባው ቢጠቅሰም ቀጣዩ ግን እጅግ አስፈሪ ነው። በምን ሁኔታ ይህ ዝርግ ፖለቲካ ሊገራ እንደሚችል ፈጣሪ ይውቀው። እዬጨነቀኝ ነው። ከነሴራው የተቀላቀለው መንፈስ ከአገር ውስጥ ሽምቅ ተዋጊው ጋር ተቀይጦ የአጥቂነት ሥራውን እዬሠራ ነው። ንፁሃን ምን አደረጉ? በተበከለ ምግም 2000 ወገኖች ጥቃት እንደተፈጸመ በአንቦ አካባቢ ተገልጧል። በዚህ ዓይነት ስንቱ ነገር ቁጥጥር ተደርጎ ሊደረስበት ነው። አለመደብንም እኛ ሰላማዊ፤ ምህረት፤ ይቅርታ ፍቅር ብሎ መልካምነት። ግድለው፤ እስራው፤ አፍነው፤ አፈናቅለው ነው የተኖረበት። የሆነ ሆኖ ይህ አስደንጋጭ ዜና ነገን እንዲያምጥ ያድርገዋል። ከበደኝ። ይህ ምስኪን ፍጥረት ምን ያድርግ? ከስንት ይቆራረጥላቸው? ያ ሌት እና ቀን ተባክኖ በውጭም በአገር ውስጥም መንፈስን ለማስተካከል የተደረገው ዘመቻ በአዲስ ቀውስ ፈጣሪ እና አምራች ሃይል እና ጉልበት እንዲናድ፤ እንዲቀዬጥ፤ አንድነቱ እንዲበጠበጥ ተተግቶ እዬተሠራበት ነው። ለዚህ እኮ ነው አንድም ተፎካካሪ ፓርቲ ሥራ ሊጀምር ፈቃደኛ ያልሆነው። ውስጥ ለውስጥ አድማው አለ። መፍንቅለ መንግሥት። በሌላ በኩል ከኢትዮ ሱማሌ የተፈናቀሉ ምንዱባን ባህርዳር ላይ የክልሉ የጥበቃ ሃይል ሊያግዛቸው ሲገባ ጥቃት እንዳደረሰባቸው ዘገባው ይጠቁማል። ይኸው ነው ሴራው። ሌላውን ወርቅ ትሸልማለህ፤ ካባ ትደርባለህ በሰላም አገር ሲዘባነን የነበረውን ተመችቶት ደልቶት የኖረ

ዶር ደብረጽዮን ምን እያሉን ነው? ስታውሱን ካሉ በጥቂቱ .. ገመናችሁ።

ምስል
ዶር ደብርጽዮን  ምን አያሉን ነው? „አቤቱ ዝናህን ሰምቼ ፈራሁ፤ በዓመታት መካከል ሥራህን ፈጽም“ ትንቢተ ዕንባቆም ምዕራፍ ፫ ቁጥር ፪ ከሥርጉት©ሥላሴ 18.09.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድንድ። ·        መነሻ ምርኩዝ። https://www.zehabesha.com/amharic/archives/94329 የትግራይ ክልል መንግስት ለዶ / ር አብይ የፌዴራል አስተዳደር ማሳሰቢያ ላከ ከትግራይ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የተሰጠ መግለጫ 17.09.2018 አንዳንድ ሰዎች „ወያኔ ይሻላል“ እያሉ ነው። ቃሉ አባባሉ እራሱ ያሳፍራል። ከጭካኔ ጭካኔ ምን ይመረጣል? ከሞትስ ሞት ምን ሌላ ሞት ይመረጣል፤ ከኢ- ሰባአዊነት ኢ - ሰብዐዊነትስ ምኑ ይመረጣል? ከአረመኔነት ምኑ ሌላ አረመኔነት ይመረጣል፤ ሁሉም ጸረ ሰው፤ ሁሉም ጸረ ተፈጥሮ፤ ሁሉም ጸረ እግዚአብሄር ናቸው።  እስታውሱን ከሆነ ትንሽ እስኪ ከጭካኔያችሁ ምስል ጋር በምልሰት ዋንጫችሁን አንስታችሁ የተለመደውን ፈንድሻ ርጫ ርጫ ማድረግ ነው  ..ለዛራችሁ፤ ለገዳዩ አውሌያችሁ፤ ለአረመኔው ቆሌያችሁ። ምን አለ ዝም ብትሉ ደግ መሪ ሰጥቷችኋዋል አትንኳቸው፤ አትድረሱባቸው፤ እንኳንስ የሰው የዶሮ ደምም አይደፍሩም ትብሎላችኋል፤ ታውጆላችኋዋል። ዘር አላጠፉም ተብሎ ተመስክሮላችኋዋል የሰማዩን ቁጣ መስቀረት ከታቻለ፤ ልጅም ካወጣ ...   ወያኔ ሃርነት ትግራይ በእያንዳንዷ ቀን ሲገድል፤ ሲዘርፍ፤ ሲያሳድድ፤ ሲያ ሰድ ድ፤ ሲደፈር፤ ሲጨክን ነው የኖረው። ለመሆኑ ወያኔ ሃርነት ትግራይን እንደ ሰውስ፤ እንደ ድርጅትስ ማዬት ይቻላልን? በተብዕት ዘር ማፍሪያ ሽቦ ሰዶ የሚአሰቃይ? ከእባብ ጋር ሰዎችን የ

ጥምልምል በቁልፍልፍ።

ምስል
ጥምልምል በቁልፍልፍ፤ ጥምንምን በትልልፍ። „እግዚአብሄርን በኃጢያታቸው  እንዳሳዘኑት እሱም ቸል እንዳላቸው እንደቀደሙ ሰዎችም አትሁኑ በጥፋት  ውሃም ያጠፋቸው አሉ።“ መጽሐፈ መቃብያን ካልዕ ምዕራፍ ፲፲ ቁጥር ፮ ከሥርጉተ©ሥላሴ 18.09.2018 ከጭምቷ ሲወዘርላንድ። መነሻ። የኔዎቹ እንዴት ናችሁ ኦቦ በቀለ ገርባን ትሁት እና ታዛዥ አድርገን መሳላችን፤ ለዛም መታገላችን አይቆርቁረን። የሳቸው ህሊና እስከ መቼውም እረፍት የማይሰጠው የመልካም ነገር ዕዳ አስቀምጠናል። እርግጥ እጅግ የሚያሳስበኝ ጉዳይ ደግሞ አለኝ፤ ከልዕልት ጽዮን ጋር በነበራቸው ቆይታ ልጆቻቸውንም በሳቸው አምሳል በነፃነት ታገይነት መንፈስ አስርጸው ማሳደጋቸውን አዳምጬ ነበር። አሁን እንዛ ቀንበጥ እና ዕንቡጥ ልጆች ያስስቡኛል የነገ ዕጣ ፈንታቸው። ምክንያቱም ዛሬ እምናያቸው ኦቦ በቀለ ገርባ ልጆቻቸውን እንዴት እንዳሳደጉ እንዴትም እንደቀረጹ አስተርጓሚ ስለማያስፈልገኝ። ሌላው አሁን እሳቸውን እንደ ኢትዮጵያ የመፍትሄ አካል አድርጎ የማዬቱ ለሳቸው የተሰጠው መንግሥታዊ አደራም ከእንግዲህ ውል የለሽ ነው። እሳቸው የሚታገሉት ለታላቋ ኦሮምያ ጋር ነውና።  ያን ጊዜ ደጋግሜም እንዳነሳሁን አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ታውጆ ያን ረግጠው ነቀምት ላይ ስብሰባ እንዲዛጋጅ ያደረጉትም ይህን መሰል የሰሞኑን መሰል ሁከት እና ብጥብጥ ለማስነሳት ስለመሆኑ የሰሞኑ ይፋዊ እንቅስቃሴ ይታያል። ለዚህም ነው ሲፈቱ አጀንዳ ያልነበሩ ሲታገቱ ለሚዲያ መጫኛነት የተጠቀሙባቸው። ጥምልምሉ ፖለቲካችን እንዲህ ነው። ለእውነት ሳይሆን ግርግሩ ለ እኔ ከጠቀመኝ ነው።  ለ እኔ በግልጽ ቋንቋ ማሽሞንሞን ስለማልሻ መፍንቀል መንግሥት ነው አዬሆነ ያለው። የሆነ ሆኖ ለንፅ