ልጥፎች

ከሴፕቴምበር 16, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ያላለቀ መከራ ሰርካዊነት።

ምስል
ማንዘርዘሪያ። „ክፉ አድራጊዎችን ሁሉ ጠላሁ።“ መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ ፭ ቁጥር ፭ ከሥርጉተ©ሥላሴ 16.09.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። ትናንት እና ከትናንት በስትያ ሌሎች ተግባሮችን እዬተከታተልኩኝ የተሰጡ መግለጫዎችን አዳምጥ ነበር። በመጀመሪያ የአቶ ታከለ ኡማ የአዲስ አበባ መግለጫ ከውጭ ለሚመጡ እንግዶቻችን አዲስ አበባ አቀባባል ታደረግለች የሚል ዕድምታ ነበረው።  ኦነግ እና ግንቦት 7 ብቻ ነው ወይ በስታዲዬም ደረጃ አቀባበል የሚደረግላቸውን ያሰኛል? የኦጋዴም፤ የአፋርም፤ የትግራይም፤ የአማራም፤ ኢትዮ መንፈስ ያለቸው የሲቢክስ ድርጅቶች መሪዎች እኮ ከዚህ ቀደም ገብተዋል። ምነው የዜግነት እሮብ እና ሲሶ ነበረውን ወይንስ አለውን? ሌሎቹ እኮ ከነመፈጠራቸውም አይታወቁም። በአክቲቢስት ደረጃ የኢትዮ ሱማሊያ፤ የአፋር፤ የአማራ፤ የጋንቤላ /ኢትዮ/ ገብተዋል እነሱስ ዜግነታቸው የእንጀራ ልጅነት ያህል ነውን? ለነገሩ ጠ/ ሚር አብይ አህመድ ሚሊዬነም አዳራሽ ንግግር ሲያደርጉ ሁለት የኦነግን ክንፍ ሲጠሩ፤ ሌሎችንም ሲዘረዝሩ አንድም የአማራ ድርጀት ሊሂቅ ሲጠሩ አልሳማሁኝም። አንድም የአማራ አክቲቢስት ሲያወሱ አልሰማሁም፤ ዶር አብይ አህመድ አብነት በሆኑበት በጎ አደራጎት ደግሞ አዲስ አባባ የከንቲባ ጽ/ቤት መልካም ተግባር ሲከውን ሰነባብቷል።  ለነገሩ የብአዴን የካባ እና የጃኖ ልዩ ዝግጅትን እወክላለሁ ለሚለው አማራ አብራክ እና መህጸን ለተገኙ ሊሂቃኑን ሲቀበልም ሲያሰተናገድም ክብር ሲሰጥም አልታዬም። ይህ የአቶ ንጉሡ ጥላሁን ሌጋሲ መሆኑ ባይጠፋኝም ፊት የተነሱ ዜጎች መኖራቸውን ግን ግልጥ ሊሆን ይገባል። አማራም ይህን ከታሪክ እዬተጋፋ ስለመሆኑ ማወቅ ይኖርበታል። ባይታወርነቱ ቀጥሏል ለዛውም በተደራጀ ሁኔታ። 

ቅብጥ እና ቅልጥ ያለች ወግ ቢጤ ...

ምስል
ያሰረብኝ „ምስጉን ነው በክፉዎች ምክር ያልሄደ  በኃጢአተኞችም መንገድ ያልቆመ በዋዘኞችም ወንበር ያልተቀመጠ። መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ ፩ ቁጥር ፩ ከሥርጉተ©ሥላሴ 16.09.2018 ከሰላማዊቷ ሲዊዘርላንድ። ·         እፍታ። ውዶቼ እንዴት ናችሁ ደህና ናችሁን? እኔ አለሁላችሁ። ይህ እንደግዲህ ካልተተመው 8ኛው መጸሐፌ ውስጥ ያለ ወግ ቢጤ ነው። ያው ግንቦት 7 ኢትያጵያ ላይ ዴሞክራሲን ሊሳዬን ከሄደ እንደ ሶሞናቱ ገለጣ ማለት ነው ትንፋሽ ይገኛል ማለት ይሆናል። ይህ ማለት እንገናኝ ይሆናል በመጣጥፉ፤ በትርካው በሥነ - ግጥሞ በፍቅራዊነት ፕሮጀክቱ፤ በ አጫጫር ፊልም ... ወዘተ እንደ ፈቃዱ ቤተ የቅኖች ማዕዶት ቢኖረን ተብሎ ተስልቷል። አሁን ሲዊዝሻ ነጣነቷ እያታወጀላት ነው።  በማዕቀብ - በክትር - በገደብ በወያኔነት ፍረጃው አክትሟል „የዛሬ 6 ወር ያለሰብነው እዬተባል ነው“ „መነገድ እና ትንሳኤ እኛ ነን“ ተብለን ነበር። ዛሬ ደግሞ ሌላ ጨዋታ መጥቷል። ለካንስ እንሱም በድርጅታቸው ተስፋ አጥ ኑረዋል። ሆድ ያባውን ሆነ እና የምናውቀውን እያሰሙን ነው … የሆነ ሆኖ ዕድሜ ለአማራ የህልውና የማንነት ተጋድሎ እና ለቄሮ ንቅናቄ። እንዴት ነው ብአዴን ተዚህ ላለውም ወገኖቹስ የጃኖ ገብያ ቢከፍት ምንአለበት? እይመስላችሁንም?  የንጉሡ የጃኖ ሌጋሲ ቤት ተብሎ፤ ለእኛ ደግሞ ሙለወርዷን … ወጉ እንዲህ ቀርቧል … ·         የወግ ገበታ።            ውይ ውይ ውይ … እ! እ! እ! አቃሰትኩ። አምላኬ ምስክሬ ነው በጢንብራዬ ሊዳፋኝ … ፈተለኝ። ሲፈትለኝ ዘኃም ግራም … ጥጡም … ጥጥፍሬውም የለም …. በልሙጡ ... ሊደጠኝኝኝ እም ...  ብቻ ብቻ ብቻ የዛሬው የጉድ ነው። መጥቶበታል አል

Sonst, (Gedicht)

ምስል
Sonst, „Wohl dem, der nicht wandelt nach dem Rate der Gottlosen, noch tritt auf den Weg der Sünder, noch sitz, da die Spötter sitzen“  (Die Psalmen Erst Buch 1 ፡ 1) Sergutre©Selassie 16.09.2018 (Aus der friedlichen Schweiz.) gehen … gehen… gehen fahren … fahren …. fahren reisen … reisen … reisen immer noch, immer wieder laufen… weiter und weiter die Zeit hat keine Haltstelle. Sie hat Reiselust sie wartet nicht. die Reisenden müssen unbedingt mitfahren es gibt keine andere Möglichkeit sonst werde man durchfallen ja, s… aus, die Zeit vorbei. die Natur der Zeit ist fliegen die Zeit verfliesst wie Fluss die Zeit zufliegt wie Flug die Zeit hat selbe auch keine Zeit.   Gott beschütze uns und die Welt . Danke. Eine gute Zeit.