ልጥፎች

ከጁን 9, 2023 ልጥፎች በማሳየት ላይ

Aba Giyorgise and Amahara.

ምስል
 

Enforced Disappearance) "በኢትዮጵያ እየጨመረ የመጣው ሰዎችን አስገድዶ የመሰወር (Enforced Disappearance) ድርጊት በአፋጣኝ ሊቆም ይገባል

"በኢትዮጵያ እየጨመረ የመጣው ሰዎችን አስገድዶ የመሰወር (Enforced Disappearance) ድርጊት በአፋጣኝ ሊቆም ይገባል ... የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ/ኮሚሽኑ) በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በኢትዮጵያ ውስጥ የተለያዩ አካባቢዎች እየጨመረ የመጣውን የአስገድዶ መሰወር (Enforced Disappearance) እና ተይዘው የሚገኙበት ሁኔታ ሳይታወቅ በእስር ላይ የሚገኙ (Incommunicado Detention) ሰዎችን ጉዳይ ሲከታተል ቆይቷል። ኢሰመኮ በተለይ በአዲስ አበባ ከተማ፣ በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች ከደረሱት አቤቱታዎችና ጥቆማዎች በመነሳት ሲያደርግ በነበረው ክትትል መሠረት በርካታ የአስገድዶ መሰወርን ድርጊት የሚያቋቁሙ ድርጊቶች መከሰታቸውን አረጋግጧል። አብዛኛውን ጊዜ የዚህ ድርጊት ሰለባ የሆኑ ሰዎች ከመኖሪያ ቤታቸው፣ ከሥራ ቦታ ወይም ከመንገድ ላይ የሲቪልና የደንብ ልብስ በለበሱ የመንግሥት ጸጥታና ደኅንነት ሠራተኞች ያለ ፍርድ ቤት የመያዣ ትእዛዝ ተይዘው ከታሰሩ በኋላ ወዳልታወቀ ስፍራ እየተወሰዱ እንዲሰወሩ የተደረጉ ሲሆን፤ ከፊሎቹ ከተወሰኑ ቀናት፣ ሳምንታት ወይም ወራት መሰወር በኃላ የተገኙ መሆናቸው የተገለጸ ቢሆንም፣ ሌሎች ይህ መግለጫ እስከተሰጠበት ጊዜ ድረስ በግዳጅ እንደተሰወሩ የቀጠሉ ናቸው። ከእነዚህ ተጎጂዎች መካከል የተወሰኑት ሲያዙ በወንጀል ተጠርጥረው የሚፈለጉ መሆኑ ተነግሯቸው ወደ መደበኛ ፖሊስ ጣቢያ ከተወሰዱ በኋላ የተሰወሩ ሲሆን ከፊሎቹ ደግሞ ምንም ሳይነገራቸው በጸጥታ ኃይሎች ተወስደው የተሰወሩ ናቸው፡፡ የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ “ይህ አስከፊ የሆነ የአስገድዶ መሰወር ድርጊት በአስቸኳይ እንዲቆም መንግሥት አስፈላጊውን ጊዜያዊ እና ዘለቄታዊ እርምጃዎች ሁሉ እንዲወስድ፣ የተሰወሩ
ምስል

ዬተረጋጋ ሥርዓት የሚፈጠረው በዊዝደም እንጂ በግልቢያ አይደለም። ቦጅጃው የቋንጃ የኢትዮ ፖለቲካ እና አጤ ሂደት??? #ትናንት ፈርሶስ ዛሬ አለን ማለት ይቻል ይሆን? ተፈቅዶ በፈራረሱ ትናት እና ዛሬ ላይስ #ማግሥትን ማስላት ይቻል ይሆን???

ምስል
        ዬተረጋጋ ሥርዓት የሚፈጠረው በዊዝደም እንጂ በግልቢያ አይደለም። ቦጅጃው የቋንጃ የኢትዮ ፖለቲካ እና አጤ ሂደት??? #ትናንት ፈርሶስ ዛሬ አለን ማለት ይቻል ይሆን? ተፈቅዶ በፈራረሱ ትናት እና ዛሬ ላይስ #ማግሥትን ማስላት ይቻል ይሆን??? ረዘም ያለ ፁሁፍ ነው። ትንሳኤን ለሚያልሙ ምራቃቸውን ለዋጡ የኔወች የተጣፈ ነው።   "እግዚአብሄር በአንድም በሌላም ይናገራል ሰው ግን አያስተውለውም።"   ውቦቼ እንዴት አደራችሁልኝ? በአራቱም ማዕዘን በማደምጣቸው ህውከት በሚንጣቸው፤ መረጋጋት በተሳናቸው አመክንዮ ዙሪያ ጥቂት ነገሮችን ላነሳሳ ፈቀድሁ። እንሆ ………   #እኔ ስል …… እንዲህ ……… ሂደት ሽግግር ነው። ሂደት የዘመን ልውውጥ ነው። ሰከንክም፦ በረገግክም ሂደት በራሱ ህግ እና ሥርአት ይሄዳል፤ ይተማል። ሂደት ጎዳናውን ያውቃል። በሂደት ውስጥ #አናርኪዝም ዬለም። ግጭቱ በሂደት ህጋዊ ሥርዓታዊ ጉዞ እና ሂደትንን ቀድመን እንቆጣጠረዋለን በሚሉ ዕብን መንፈስ አናርኪዝም ጉዞ ነው። የግጭቱ ስበት እና ስበቃ በመሃል አናርኪዝም ስላለ ስኬቱ ውድቀት፤ ጉም እና ትቢያ ማፈስ ይሆናል።   የሰው ልጅ እራሱን የሚመራበት ሥርዓት እና ህግ ሊኖረው ይገባል። በግሉ ማለት ነው። ያ ሥርዓት እና ህጉ ከብሄራዊ፤ ከሉላዊ ህግ ጋር ግጭት ሳይፈጥር ተስማምቶ ይሄድ ዘንድ ሂደትን ማጥናት፤ ሂደትን ማወቅ፤ ሂደት ለዘመኑ የደነገገውን ድንጋጌ ማወቅ። ዕውቀቱን ዕውቅና መስጠት ያስፈልጋል።    አንድ ሰው ተቋም ነው። አንድ ሰው ሚስጢርም ነው። ሚስጢርነቱንም ተቋማዊነቱንም መመራት፤ በቅጡ ማሰተዳደር የሚቻለው ሥርዓት መከተል ሲቻል ብቻ ነው። የሥርዓት ጥሰት የሂደትን መፋለስ ሳይሆን የሚፈጥረው የትውልድን አደራ እና ራዕይን ያፋልሳል። ሂደት በራሱ መርህ፤ በራሱ

7.2 ሚሊየን ቤቶችን እንገነባለን ወይስ እናፈርሳለን ?

ምስል
7.2 ሚሊየን ቤቶችን እንገነባለን ወይስ እናፈርሳለን ? መቼም << አብዛሀኛዎቹ የመንግሥት ሰዎች ቁርጥ ላይ እንጂ ቁጥር ላይ እስከዚህም ናቸው! >> የሚባለውኮ በምክንያት ነው! የከተማ እና የመሠረተ ልማት ሚንስቴር ከአመት በፊት ይፋ ባደረገው "ዕቅዱ" 7,200,000 (ሰባት ሚሊዮን ሁለት መቶ ሺህ) ቤቶችን በ 10 ዓመታት እገነባለሁ ብሎን ነበር ። ይህም ማለት፦ << በዓመት 720,000 ቤቶች ፤ በወር 60,000 ቤቶች ፤ በቀን ደግሞ 2,000 ቤቶችን እገነባለሁ! >> ማለት ነው! እንግዲህ ቁጥር የሚዳፈረው ተግባረ ዜሮው መንግስታችን ፤ በእስካሁኑ ልምዱ 400,000 ቤቶችን ለመገንባት 18 ዓመታት ፈጅቶበታል። አይደለም በቀን 2 ሺህ ቤት ሊሰሩ (ሊያመርቱ) ይቅርና ለፕሮፓጋንዳ ''ሰራናቸው '' ያሏቸው ዳቦ ቤቶች እንኳ ፥ በቀን 2 ሺህ ዳቦ ማምረት አልቻሉምኮ! ለመሆኑ ግን ሌላ ሌላውን ቁጥር ማግተልተሉን ተውትና ፥ ከታቀዱት 7 ሚሊዮን 2መቶ ሺህ ቤቶቹ ስንቶቹ ተመረቱ? ወይስ ደግሞ እቅዱ '' የ7.2 ሚሊየን ዜጎችን ቤቶች እናፈርሳለን!'' ነበር ወይ ?