ልጥፎች

ከጁን 22, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

Shaqiri und Xhaka, Stolz!

ምስል
Shaqiri und Xhaka, Scholz! ሻካና ሸኪሪ ኮራሁባችሁ!               ከሥርጉተ© ሥላሴ 22.06.2018                     ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ።           "እግሮች እንዳይናወጡ አረማማዴን በመንገድህ አጽና።"             (መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ ምዕራፍ ፲፮ ቁጥር ፭) ጭመቷ ሲዊዝ ዛሬ ጭምትነቷን ገፋ አድርጋ መኪኖች ሁሉ አደባባይ ወጥተው ሙሻረውን ድል እንኳን አገኘህን እያሉት ነው። ደግነቱ ቀኑ አርብ ነው። ህዝቡም በዬበረንዳው በዬመስኮቱ ሆኖ እያጀበ ነው።   ሲዊዝ ድብልቅልቅ ብላላች አልልታ በእልልታ እሰዬ … የሲዊዝ ህዝብ የሞራል ልዕልና እኮ የተለዬ ነው። ሱቅ ላይ ቀላል ዕቃ ከያዛችሁ በርከት ያለ ዕቃ ለመግዛት የተሰለፈው ያሳልፋችሁዋል። ከዬትም አገር ቆይታችሁ ሲወዝ ስትገቡ ሻንጣ ማውረድ ካቃታችሁ ይረዱችኋዋል። ልዩነቱን በደንብ ታዩታላችሁ፤ ሌላ ቦታ እኮ ትዝ አትሏቸውም፤ ሲዊዝ ግን ጠረኑ የተቀደስ ነው።   እናቶች ህፃናትን ጋሬ ይዘው ብቻቸውን ባቡር ላይ አያወጡም አያዋርዱም። ባልተፃፈው ህጋቸው የተከለከለ ነው።  መኪና ያላቸው ከሌላ አገር ወደ ሲዊዝ ሲገቡ ቀድመው እንዲሄዱ ይፈቅዱላቸዋል። ዲታውም ደሃውም ራሱን ዝቅ አድርጎ ምንም የሌለው መስሎ ይኖራል በልክ። ሁሉም ነገር በደንበር እና በዝምታ ውስጥ ነው … ለጠብ አይተጉም።   ዛሬ የምር ከልቤ አለቀስኩኝ። እዚህ ከኖርኩበት ዘመን ሁሉ ለሲዊዝ ሰቅሰቅ ብዬ ያለቀስኩበት ቀን ነው። ለሲውዝ ይገባታል ከእናትም እናት ናት። ጨምሮ ጨማምሮ ህዝቧን የሚያስደስት ድል ፈጣሪ አምላኬ ይጨምርልኝ። አሜን! ብንታመም አስታማ፤ እናዳይርበኝ አብልታ፤ እናዳይጠማኝ ሁሉን ሰጥታኝ፤ መጠለያ

የሙሳ ወፍ ዕድል ቀናት። ተመስገን!

ምስል
ጠይም ዕንቁ በጣምራ ድል የሙሳ ወፍ ዕድል ቀናት።                          ከሥርጉተ © ሥላሴ 22.06.2018                                (ከገዳማዊቷ ሲዊዝዬ)               „አቤቱ በአንተ ታምኛለሁ እና ጠብቀኝ።“ አሜን!                  (መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ ፲፭ ቁጥር ፩) ዋው ዋው ዋውውውው! ለዛውም ሦስት አደገኛ የመረብ ዕድል አምልጧቸው እኮ ነው አረንጓዴ ዕንቡጦች ዛሬን በድል ያቀለሙት። ተመስገን። ብዙ ጊዜ ናይጀሪያ ከጭዋታ ውጪ ሲሆን እኔን ጨምሮ የሙሳ ጉዳይ ብዙ ሰው የሚያዝንበት ነበር። የዛሬው ጨዋታ የሙሳ ወፍ ዕድል ቀናት። አይስላድንዶች ከእነታዳሚቸው እጅግ ተወዳጆች ናቸው።  የጋራ የወል ቃናዊ ድምጽ አላቸው፤ ሌሎች ቡድኖች ሲያሸንፉ የእነሱን ሲቀዱ ፈጽሞ አያማርባቸውም ባለቅኔው ጠ/ ሚር ዶር አብይ ሲዳማወችን "ፊትችሁ ያመራል፤ ደስ ትላላችሁ" ነበር ያሏቸው አዎ  በአግር ኳስ ጨዋነት የአይስላንድ ቡድን ደጋፊ ሞራሊዊ ነው። የፍቅራዊነት ተፈጥሯዊ መርህ ናሙና ናቸው። መሸነፋቸውን በደስታ የሚቀበሉ ፍጥረቶችም ናቸው። ብስጭት የላቸወም። ለስላሶችም ናቸው። 80.50 ላይ ፔናሊቲ እድል አግኛቷል የአይስላንድ ቡድን። ፔናሊቱ ግን ተሳተ። ዛሬ ወፏ ለጠይም ዕንቁ ቡድን አዳላች ልብል ፈረደች። ፈረደች ይሻላል አይደል? የአፍሪካ ቡድን ሁልጊዜ አጨራረስ ላይ ችግር ነበረበት። ይህ የወል ፈተና ነበር። ዘንድሮ ግን በጣም የተሻሻለ ሁኔታ ታይቷል። የሞሮኮ ቡድን ቢሸነፈም ጠንካራ ነበር። የግብጹ ወደር የለሽ ነበር። ያው ኳስ አንድንድ ጊዜ ዕድልም ነው። ሴኒጋሎች የጀርምንን ኤፍ ፋው ቤ አይነት ፈጣኖች ናቸው። እነሱም አሸንፈዋል። አሁን ናይጀ

ዕድሜ ለዶር አብይ አህመድ ልበ ብርሃን መንፈስ!

ምስል
ዕድሜ ለዶር አብይ አህመድ ልበ ብርሃን መንፈስ አቅሌን ወሰደው። ከሥርጉተ  ©  ሥላሴ 22.06.2018 (ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ።) "የህይውትን መንገድ አሳዬህኝ፡ ከፊትህ ጋር ደስታን አጠገብኽኝ፤                   በቀኝህም የዘለ ዓለም ፍሰሃ አለ።"                (መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ ፲፭ ቁጥር ፲፩) መቼም እኔ በህይወቴ የምወዳቸው ሁለት ነገሮች ሥነ -ጥበብ እና እግር ኳስ ጨዋታ ናቸው። ያቺ ድንቡልቡል በተደሰቀች ቁጥር ከንበል ቀና፤ ከፍ  እና ዝቅ ባለች ጉናዊ ንጥረቷ ቁጥር ሚዜና እና ሙሽራዋን እዬለዋወጠች ወክ እንዲህ ባለች ቁጥር ነፍሴም ብን ትር ይልላታል። ለዚህም ይመስለኛል ጥቁር ነጭ በጣማራ የሁለመናዬ የቀለም ምርጫ የሆነው። ለሥጋዬ ማለት ነው። ለነፍስ አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ነው። ጀርመን በ2010 በድንቅ የመቻቻል ልቅናው፤ በ2014 ደግሞ በዋንጫ ባለቤትነቱ ውስጤ እንዲቀመጥ ሆኗል። ከሁሉ በላይ ግን የባስቲ እና የ የኡዚል ቅንንት የተለዬ ነው ለእኔ። ናሙናነታቸውን መጸሐፌ ውስጥ ሁሉ ጽፌዋለሁኝ። ከኢጎ ጋር የተፋቱ ናቸውና። የመንፈሱ ሃብት ደግሞ የመቻቻል ሉላዊ እናት የጠ/ ሚር አንጅላ ሜርክል ብቃት ልቅና እና  ለዓለም ግፉዕንን ለማድመጥ የሚሄዱበት መንገድ እና ትህትናቸው ጀርመን ልክ እንደ ጎጃም የልቤ ማህደር እንዲሆን ሆኗል። ዘንድሮ የጀርመኑ ጨዋታ እጅግ በረዷማ ነበር። ጀርመን በቶማስ ሙለር አምልኮቱ በ2014 የአውሮፓ ዋንጫ ውደድር ዕድሉን አጥቷል። ቶማስ ሙለር የኮከቦች ኮከብ ተጫዋቻቸው ቢሆንም ከተገባው በላይ አምልኮው ግን ለእኔ የተገባ አልነበረም። እኔ ይህንኑ በ2014 ጽፌላቸው ነበር። የቶማስ ሙለር አቅም ኡዚል እና ባስቲ ናቸው። ለ2010 ለወርቅ ጫማ

ቅንነት ሲከብደን ተስፋችን እዬራቀን ይሄዳል!

ምስል
ቅንነት ሲከብደን ተስፋችን እዬራቀን እንደሚሄድ ልብ አላልነውም። ከሥርጉተ ሥላሴ 22.06.2018 (ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ።) „በጸሎት ስናገር አስቀድሜ በራዕይ አይቼው የነበረው ሰው ገብርኤል እንሆ እዬበረረ መጣ፤  በማታም መሥዋዕት ጊዜ ዳሰሰኝ።“ (ትንቢተ ዳንኤል ምዕራፍ ፱ ቁጥር ፳፩) „የ40 ቀኑንም መንገድ 40 ዓመት አታድርጉት። የባለቅኔው ጠ/ሚር አጽህኖታዊ ቃለ ምህዳን። እንዴት ግን ይክበደን ቅንነት ? ተሸከሙኝ አላለም እኮ። እዘሉኝ አላለንም እኮ። እቀፉኝ አላለንም እኮ። አሽኮኮ አድርጉኝ አላለንም እኮ። ቅንነት አይከፈልበት፤ አይወጣ አይወረድበት። ወረፋ አይጠበቅበት። ውቅያኖስ አይሻገሩበት። ራሽን አይመደብበት ግን ስለምን ከበደን ? ግን እኛ ስለሰው ልጅ ስንፈጠር፤ እኛም ሰው ናችሁ ስንባል ግን ስለምን መልካም ነገርን መድፈር ተሳነን ? ቅን ብንሆን ምን ይቀርብናል ? ሰዎች ሲገናኙ ጨጓራችን አቃጥለን። ሰዎች ሲሰባሰቡ አንጀታችን ቆርጠን። ሰዎች የውስጥ ሰላማቸው ሲመልስ ራስ መርዘናችን ተነስቶ ግን እኛ ምንድን ነን ? እውነት ለመናገር የእኛን ህዝብ ከመምራት ምን እንደሚሻል መድፊያውን ጨረሱልኝ በሥርጉተ ሞት። አንድ ቅን ባተሌ በሥንት ዘመን ኢትዮጵያ በቃሽ ብሏት ፈጣሪ አምላክ፤ በዚህ በተዘባረቀ ውጥንቅጡ በጠፋበት ጨቀጨቃማ ዘመን ሙሴ ሰጥቷት ለሁሉም በቃሉ መሰረት ልቡን ሸልሞን፤ ህሊናውን አብርክቶን፤   ወጣትነቱን ሰጥቶን፤   እኛ ግን የሰጠንን ቅንነት መልስን መመገብ ቀርቶ ቅንነቱን ማድመጥ ተሳነን። በቃኝ እንደፈለጋ