ልጥፎች

ከሴፕቴምበር 17, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

የኢትዮጵያ መንግሥት ለስትራቴጂ ብቻ የሚፈለግ ከሆነ ...

ምስል
ዓይን። „የፈረደብህ በግፍ እንዳይደለ ትገልጥ ዘንድ ስለ ሰው ሁሉ የሚያስብ ካንተ በቀር ሌላ ፈጣሪ የለምና፤ ስለ በደለኞች፤ ሰዎች ለመከራከር ወደ አንተ የሚደርስ ዳኛ ማነው።“ መጽሐፈ ጥብብ ምዕራፍ ፲፪ ቁጥር ፲፫ ከሥርጉተ©ሥላሴ 17.09.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ።    ·        መነ ሻ። „በአሰላ ከተማ ነዋሪ የሆኑ የአማራ እና የሌላ ብሔር አባላት የሆኑ የክርስትና እምነት ተከታዬች የመስቀል በዓል የደመራን ዝግጅት ተከትሎ ውጥረት እና ውክቢያ ውስጥ እንደሆኑ ኑዋሪዎቹ ለልሣነ _ ዐማራ ገልፀዋል።“ መስከረም 04/2011 ዓ . ም https://www.facebook.com/AmharaPress/?__xts__[0]=68. መነሻዬ የለጠፍኩት ጉዳይ ነው። ተያያዥ ጉዳዮችንም አክላለሁኝ። ኦቦ በቀለ ገርባ ስትራቲጂካዊ የ150 ዓመት ትግል ነፃነትን አሳዬን፤ የሞቱት ተነስተው ባዩልን ባይ ናቸው። ነገም ለስትራቲጂ ከሆነች ኢትዮጵያ የምትፈለገው ምን አስኪሆን ይሆን የሚጠበቃው የ ኢትዮጵያ መንግሥት የአብይስ ካቤኔ? ... ወደ ቀደመው ስገባ ዛሬ ጥዋት አንድ መሰረታዊ ነገር ከልሳነ አማራ ሚዲያ አዳመጥኩኝ። አሰላ ላይ መስቀልን ለማክበር ስጋት እንዳለ። አሰላ ላይ ብቻ ሳይሆን ቄሮ በተዳረጀባቸው አካባቢዎች፤ ጄኒራል አቶ ጃዋር መሃመድ በሚመራቸው ኔቶች ሁሉ መሰል ስጋቶች ይኖራሉ። ስጋቶች ካሉ ልዑል እግዚአብሄር የማያውቀው ስሌላ ቤት መቀመጥ ነው። በነገራችን ላይ አሰላን አየኋዋት ምንም ለውጥ የላትም። በዚህ  አይነት ጢቾ፤ አምኛ፤ ዲክስስ፤ ሴሩ ምን ላይ ይሆኑ እል ለነበረው ግብረ ምላሽ ሰጥቶኛል። የሆነ ሆኖ እኔ ለአሰላዎች የምለው አንድ መሰቀል ባይከበ

አዲስ አበቤ ሆይ ይቅናህ!

ምስል
ለዘላቂ ህልውና አይ ተመራጭ መንገድ ነው። „ጽኑ ፍለጋ ታሳያለህና ወደ መርከብም በመውጣት ኖኅን አድነሃልና።“ መጽሐፈ ጥበብ ምዕራፍ ፲፬ ቁጥር ፬ ከሥርጉተ©ሥላሴ 17.09.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ ቀጣዩ የአዲስ አባባ ዕጣ ምን ይሆን?  ከአልጎሼ አይጠራም። ብራቦ አዲስ አባባ! ህልውናህን የሚጠ በ ቀው በአቅምህ ልክ ነው። ክብርህ የሚጠ በ ቀው በህሊናህ ልክ ነው። መኖርህ የሚረጋገጠው በጥበባዊ የአይ ተጋድሎህ ልክ ነው። አዲስ አበቤ ሆይ! የእኔ አዲስ አባባ ብለህ መነሳትህ የተገባ እና ፍትኃዊም ነው። አዲስ አባባ የእኔ፤ የአንተም፤ የእንቺም፤ የእርስዎም ናት ብለህ መነሳትህ መልካም ነው። ተቋማዊ ካልሆነ ግን የወረት ነው የሚሆነው። ጤዛ! አዲስ አበቤ ሆይ! አቅምህ ዝምታህን ጥሶ መውጣቱ ጎሽ የሚያሰኝ ቢሆንም ይህን አቅምህን ወደ ባለቤት ያለው ተቋም ማሰደግ ግን ግድ ይለሃል። ተጋድሎው በዚህ መልክ እንደ ሳሙና አረፋ ተኩረፍርፎ መቅረት ሳይሆን 50 ዓመት በትጋት እና በታታሪነት ተዶልቶ 27 ዓመት ተመስጥሮ የቆዬው ለመደራደሪያነት የነበረው የአንተ የህልውና ክስመት ድንጋጌ ነበር። የአንተ የቁም የቀብር ሥርዓት ነበር። የአንተ የብትን አፈር ለማኝነት ሌጋሲ ነበር የ50 ዓመቱ የታጋድሎ ዝክረ ድንኳን። አዲስ አበቤ ሆይ! ህልውናህን ከነገ ባሻገር ማዬት፤ ከማግስት ባሻገር ማድመጥ፤ ከበስቲያ በላይ በርቅት ገና ላልተወለዱት፤ በጽንስም ላልታሰቡት ልጆች እና የልጅ ልጆችህ ስለሆኑ ዛሬ ብቻ ሳይሆን በተከታታይ ሳትሰለች፤ ፈጽሞም ሳትደከም በጀመርከው መልክ ትግልህን አቀናጅተህ በትእግስት፤ በማስተዋል፤ በፍር   ኃ እግዚአብሄር፤ በፈር ኃ አላህ ማድርግ ይኖርብሃል። አዲስ አበቤ ሆይ!

ዝርግነት የት ያደርስ ይሆን?

ምስል
ክፍተት ጎዳና ላይ … „ዳዊት በእግዚአብሄር አመነ፤ በእሱ አምኗል፤ መጠጊያ ሆነው። ከንጉሡ ከሳኦልም እጅ አዳነው።“ መጽሐፈ መቃብያ ቀዳማዊ ምዕራፍ ፳፩ ቁጥር ፩ ከሥርጉተ©ሥላሴ  17.09.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። ·        ውዶቼ የዛሬ ጹሑፌ በመደዴ ነው የሚከድበት። መቼም ይህን የመሰለ ያለተሳበ ሲሳይ ሲገኝ በጸሎት፤ በሰጊድ፤ በሱባኤ፤ በድዋ መቀበል ግድ ነው እያልኩኝ ብዙ ጊዜ ጽፌያለሁኝ፤ ምን ያህሉ ቅን ወገኔ በዚህ ጉዳይ ተመስጦ እንደነበረው አላውቅም። በሌላ በኩል ወንበሩ ባዶ ነው እያልኩ ስጽፍም ነበር። ግማሽ ፊት አይቻለሁኝም ብዬ ነበር። ያ ንጊዜ ያ ባለ ግማሽ ፊተኛ ውጭ አገር ነበሩ። አሁን ገብተዋል። በሌላ በኩል ዶር ለማ መገርሳ የት ናቸው እያልኩም በዬጹሑፎቼ እጽፍ ነበር። አሁንም ደግሜ ይህን ጥያቄ ማንሳት እገደዳለሁኝ።  ዶር ለማ መገርሳ በፖለቲካ ሙሉ አቅማቸው እና ብልህነታቸው እንዲሠሩ ተፈቅዷል ወይንስ ተገለዋል? ወይንስ ይታያል ጉዱ የቤተዘመዱ ላይ ናቸው? ኦህዴድ ወደ ሥልጣን ሲመጣ በበዛ ፍሰሃ እና ደስታ ሆኖው ቃለ ምልልስ አድርገው ነበር። አሁን በቅርቡ የዓመቱ ምርጥ የበጎ ሰው ሽልማት ላይ ባደረጉት ንግግር ደግሞ በዛ ውስጥ እንደሌሉ እንኳን ደስ አለዎት ልል በፃፍኩት ላይ አመላክቻለሁኝ። አቶ ጃዋር መሃመድን በሚመለከት እግዚአብሄርን ባገኘው የምጠዬቀው ስለምን እንደ ፈጠረው እጠይቀው ነበር ብዬ ሰብዕናው አስቂኝም አሳዛኝም ሳይሆን የሲቃ ነው። ቀለሙም ግራጫማ ነው ብዬ ጽፌም ነበር። አሁን ባሉት ነገሮች ዙሪያ ለጊዜው ስርክክር ቢልም በጥራት መውጣቱ አይቀሬ ነው። በዶር ለማ መገርሳ እና በዶር አብይ መሃከል ክፈትት ከተፈጠረ ብቻ ለውጡ አደጋ ሊኖረው ይችላል ስል