ልጥፎች

ከጁን 15, 2024 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ድብድቡ መቼ እንዴት ይቁም።

ምስል
  ድብድቡ መቼ እንዴት ይቁም። "አድርገህኛል እና አመሰግንኃለሁ።"   ክወና ነው። ለምን ማፍራት ተስኖን #ፈሰስን ? #ቀዳዳችን ስለምን በረከተ? #ቦክሱስ መቼ ይቁም? #ክፋነት መቼ ይቀበር? በራስ ላይ መዝመት ከተቻለ ሁለንም ብትክ ጉዳዮች ቀብረን ወደ ቀደመው ዊዝደማችን ጉዞ መጀመር እንችላለን። ዊዝደማችን ለተፈጥሯችን ዕውቅና ሰጥቶ በሱ ውስጥ ለመኖር መፍቀድ ነው። ወጪ አይጠይቅም። ትልም አይጠይቅም። ከራስ ጋር መታረቅ ብቻ ቁልፋን የመፍትሄ ትልምን ያስረክበናል። ስህተት ውስጥ ትናንትም፤ ዛሬም ብቻ ሳይሆን ስህተትን ለማስቀጠል ትጋታችን ሊገታ ይገባዋል። ሁሉም በግድፈት ተነክሮ ነው የኖረው። በሌላ በኩል ደግሞ ሁሉም አለኝ የሚለው አቅም አለው። ለድክመቱ መሻሪያው የራስ ዳኝነት ነው። ለአቅሙ ደግሞ በውጭጭ አቅም ቅንነትን መግቦ አገርን፤ አደራን፤ ትውልድን ማዳን ይገባል። የታሠሩ #እስረኞች ሁሉ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ሊፈቱ ይገባል። #ተኩስ #አቁም ሁሉም ሊያውጅ ይገባል። አቅምን ንቆ ከመነሳት ለአቅሙ ዕውቅና ሰጥቶ #በልኩ #ትኩረት ሊሰጥ ይገባል። #እላፊ መሄድም አይገባም። ስድብ፤ ማዋረድ፤ ማቃለል ለምን??? መውደቃችን ከውስጥ መቀበል አለብን። በመውደቃችን ልናፍር ይገባል። የሚሠሩ መልካም ነገሮችንም ዕውቅና መስጠት ይገባል። ግን ምንም ዓይነት ሥልጣኔ ከሰው ልጅ ህይወት፤ የመኖር ዋስትና በላይ ሊታይ አይገባም። ፈጽሞ። በጣም ስጋት አለኝ። የአማራን ህዝብ #አቅሎ የማዬት ፖለቲካ። በፍጥነት ሊታረም ይገባል። የሰይጣን ጆሮ ይደፈንና " የአማራ ህዝብ እገነጠላለሁ" ካለ ኢትዮጵያ #ባላ የሌለው ቤት ትሆናለች። የመካከለኛው ምስራቅ ፖለቲካም ሙሉ በሙሉ ይቀዬራል። ብዙ ያልነገርኳችሁ ተሳትፎ አለኝ። ብቻዬን የሠራሁት።

"WORLDFIRST"

ምስል
  "WORLDFIRST" የጨዋታ ሰዓት እረፍት እና ተጨማሪ ደቂቃወች ታክለው። 21.02 - 22.56 ቀን 14.06.2024   ዛሬ በጀርመኑ ሙኒክ አሪና ስኮትሾቹ እና ጀርመኖች ከምድብ #Aየ2024 የእግር ኳስ ውድድር የመክፈቻ ግጥሚያቸውን አካሄዱ። ቀዝቀዝ ብሎ የጀመረው ጨዋታ በጀርመኖች 4 ጎል በአንድ ቅጣት ምት 5 ለአንድ በሆነ ውጤት ጨዋታው ተጠናቋል። ጀርመኖች እግር ኳስን ከብሄራዊነት ጋር አዋህደው ስለሚዩት ልዩ የህሊና አቅም አይባቸዋለሁ።   ዛሬ ቀዝቀዝ ብሎ በተጀመረው እግር ኳስ ውድድር ስቲዲዮሙም አልሞላም ነበር። የባዬር ሙንሽንን የፍፃሜ ውድድር ያህል እንኳን ደምቆ አላዬሁትም። የሆነ ሆኖ የጀርመኖች ቀደምት ጎል ጠባቂ አማኑኤል ኖዬር፤ ቶኒ ሙለር ከነባሮቹ ተጫወቾች አይቻለሁ። አብዛኞቹግን አዲስ እና ወጣቶች ናቸው። አሰልጣኙ እራሱ ወጣት ናቸው አዲስም።   ጀርመኖች የመጀመሪያውን የጨዋት ክፍለ ጊዜ ሦስት ነጥብ አስቆጥረው ነበር የተጠናቀቀው። የቅጣት ምቱን ማግኜታቸው ብቻ ሳይሆን ስኮትሾች አንድ ተጨዋች በቀይ ካርድ ተቀጥቷል። ሁለተኛው ክፍለጊዜ አንድ ተጫወቻቸውን ስኮትሾች ሚስ ቢያደርጉም ለአንድ ጎል በቅተዋል።    ደጋፊወቻቸውም ትንሽ ተነቃቅተው ነበር በሁለተኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ጀርመኖች ሁለት ግብ በማስቆጠር 5 ለ 1በሆነ ውጤት ጨዋታው ተጠናቋል።   ጀርመኖች መጀመሪያ ዕድል ከቀናቸው ይጠነክራሉ። መጀመሪያ ጎል ከተቆጠረባቸው ግን ይዝላሉ። እንደ እረጅም ጊዜ ተከታታይ በዚህ ዙሪያ አሰልጣኞቻቸው ቢሠሩ መልካም ይመስለኛል። የመጀመሪያ ጎል ማስቆጠር ጥረት ማጠናከር ወይንም ጎል ከተቆጠረባቸው መጀመሪያ ላይ ሳይዝሉ ጠንክረው መቀጠል።    ዕውነት ለመናገር ያ ደማቁ የአውሮፓ እግር ኳስ ጨዋታ አይመስልም። የበረደው ነበር። ዓለም ትቅደ

#አማራነት #ወንጀል #አይደለም።

  #አማራነት #ወንጀል #አይደለም።   ለዓላማቸው #የማይሰበሩ ሳተናወች። ዕውነት ይምራኝ ብለው የፈቀዱ #የብዕር #ትጉኋን አማራነታቸው ብቻ ያሳሰራቸው #የነፃነት ዓራት ዓይናማወች። ያልተበገሩ የማይበገሩም። የጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ ፀረ አማራ አስተዳደር ፊት ለፊት የሞገቱ ደፋሮቹ። አይዟችሁ ውዶቼ እንደ ደመነ አይቀርም ይበራል - ይፈካል። አማራነት ወንጀል አይደለም። ግን የእኔ ውቦች እንዴት አደራችሁልኝ? ሥርጉ 15/06/024 #አማራነት #ይከበር ! #አማራነትን #መበቀል #ይቁም ! #ዕውነት #በመርኽ #ያሸንፋል ።

ፋኖሻ ባንክ #አይዘርፍም። #ሲያምራችሁ ይቅር። ማጣፊያ ሲያጥር የሞገድ ጋዜጣ ትዕይንትን መዘዝ።

ምስል
    # ፋኖሻ ባ ንክ #አይዘርፍም ። #ሲያምራችሁ ይቅር። ማጣፊያ ሲያጥር የሞገድ ጋዜጣ ትዕይንትን መዘዝ። #ፋኖ #ማንነቱን #አይዘርፍም ። ፈጽሞ። ፋኖሻ #ኢትዮጵያን ያከብራታል ያስከብራታል እንጂ አይዘርፋትም። የአማራ ሕዝብ የዘረፋ ታሪክ የለውም። "የቤትህ ቅናት በላኝ።" ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ አሊ በውጭ አገር ፈሰስ አድርገው የያዟቸው አገር ቤት ለጠቅላዩ ሥልጣን የሚታገሉ የመሹ አሉ። እኔ አውቃለሁ ይህን። ሙሉ 6 ዓመት እኔን መዳፋቸው ውስጥ ለማስገባት ታክተዋል። ግን አልቻሉም። ፋኖ አደራጀን ብለው አብሬያቸው እንድሠራ ጠይቀውኛል። ህሊናዬን እንዳከራይ። መታሰቡ እራሱ ይገርመኛል። እራሴን አፍርሼ በደራሽ ግርግርግር እንደማልጨባረቅም ልቦናቸው ያውቀዋል። የሆነ ሆኖ ፋኖ ሰማይ ዝቅ ምድር ከፍ ቢል የህዝብ ገንዘብ ይዘርፋል ብዬ አላስብም። ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ አይደለም ኢትዮጵያን ታላቋን አሜሪካ የሰለሉ እኮ ናቸው።ግዑዝ አካል የሰላም ሚር ብለው፤ ባልተፃፈ ድንጋጌ ከኤርትራ ጋር ተስማማሁ ብለው ዓለምን አላግጠውበት እኮ የመጀመሪያው የሰላም የኖቤል ኢትዮጵያዊ ተሸላሚ ሆነዋል እኮ። አይደለም በሚገዙት አገር። ቀርቶ። የሞገድ ጋዜጣ ልበ ወለድ መሞከሪያ ጣቢያ ኢትዮጵያ ካደረጓት ሙሉ ስድስት ዓመት። ሴራው እና ዜናው እኩል ይወጣል። 100 ቀናቸው እራሱ በሞገድ ጋዜጣ ትዕኝት የተቃኜ ነበር። እኔ እምነግራቸው ይቅርበወት ነው። ፋኖ መነፈሱ የሚሊዮን ድምጽ ነው። መቼውንም አያሸነፋትም። እርስወ ግን ይሸነፋሉ። መልካሙ ነገር ድልዝልዝ ያለው በሴራ ጉዞ ታርሞ ወደ ዕውነት መቀራረብ ነው የሚበጀው። የህዝብ ዕንባ የጠራው መንፈሱ ትሁት፤ ቅን ገር እና ቆፍጣና ነው። የቀናውም ይሄው ቅንነቱ እና ፍፁም ታማኝነት ነው። ስርቆት ዝርፊያ የአማራ ህ

ጥሳም።

  ዕውነት አንደበትን #አስገድዳ #ታስከፍታለች ። #ዝምታን ጥሳም። ሥርጉ2024/06/15

#ትቀጠቅጥማለች።

  በቀል #ትቀጣለች ። #ትቀጠቅጥማለች ። ሥርጉ2024/06/15

#የፈካ

  ዕውነት አያኮርፍም። ዕውነትም #አያድምም ። ዕውነት ባህሬውም ተፈጥሮውም #የፈካ #ያስቻለው #የተደሞ #ምዕራፍ ነው። ሥርጉ2024/06/15

እንዲያውም

 ዕውነት #ውድድር #ፋክክር ውስጥ ትውር አይልም። እንዲያውም ዕውነት ምንም ዓይነት #ፕሮፖጋንዳ ፤ የትኛውንም ዓይነት ፕሮፖጋንዲስት ፈልጎ አለማወቁ ልዩ #ክስተት ያደርገዋል። ሥርጉ2024/06/15

#መትነን

  የሰው ልጅ ዕውነትን ገፍቶ ስለምን ዕብለትን እንደሚያስጠጋ አይገባኝም። #እንዲገባኝም #አልፈቅድም ። ለምን? በወናነት መኖር ስለማልሻ። ዕብለት እኮ #ቀፎ ነው። ዕብለት #ወናነት እኮ ነው። ምን አለኝ የሚለው አለው አይዋ ዕብለት? #ብን #ትን ብቻ። የነጠፈም ነው። ለአደራም፤ ለትውልድ ቀርቶ ለራሱም #መትነን ነው ነገረ ስራው። ሥርጉ2024/06/15

#ፈረስ #በኋላ #እግሩ

  #የኢትዮጵያ #ፖለቲካ #ባህል #ፈረስ #በኋላ #እግሩ #ሲጋልብ #ዓይነት #ነው ። #ዛሬም #ድብድብ #ነገም #ድብድብ ። የዱላው #ክትክታ አለማለቁ ይገርመኛል። አልቦሽ። ሥርጉትሻ2024/06/15

#ግሽፈት

 የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ብቻ አይደለም #ግሽፈት ( #ኢንፍሌንሽን ) የገጠመው። የኢትዮጵያ ፖለቲካ ባህልም ( #ኢንፍሌሽን ፤) #ግሽፈት ገጥሞታል ብዬ በጽኑ አምናለሁ። ሥርጉ2024/06/15