ልጥፎች

ከኦገስት 12, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ፈተና!

ምስል
ከዶር ገዱ አንዳርጋቸው የክብር የእራት ግብዣ ማግሥት ቀራንዮ! „ስለ ኃጢያትህ ንሰሃ መግባትን አትፍራ።“  ምዕራፍ ፭ ቁጥር ፭ ከሥርጉተ©ሥላሴ 12.08.2018  ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። ይህን የምታይ እናት፤ ይህን የሚያዩ ልጆች፤ ይህን የሚመለከት የውጭ ዜጋ ዛሬ ምን ሊሰማው እንደሚችል መገመት ይከብዳል?  መቼ ነው ከሃዘን የኢትዮጵያ እናቶች የሚወጡት? መቼ ነው ከዚህ እጅግ ከሰው በታች የሚያደርጉ ዘግናኝ አገዳደል እና ውርዴት የሚወጣው? እኔ ኢትዮጵያዊ ነኝ ለማለት ሁሉ እያሰፈረኝ ነው። የቄሮ ንጉሥ አቶ ጃዋር መሃመድ ለአሱ ንግሥና የተደረገ የቀረበ ገጸ በረከት ነው የሰው ደም ሊቀርበልት ስለሚገባ። የሚገረምው እና የሚደንቀው በተሰቀለው ወገኔ ዙሪያ ቀርበው የአገዳደሉን ትርኢት እዬተመለከቱ ፌሳታቸው የሆኑ ወገኖቼ ደግሞ መኖራቸው ነው። ፖሊስ የሚባል የለም ከአቅራቢያው?    ምን ይባላል ይሄ የሰው አገር ወይንስ ምን ይባል? እንዴት ወገነህ እንዲህ ሆኖ ሲንጠለጠል አዬትህ ተኝተህ ታድራለህ? ምግቡስ ከጉሮሮ ይወርዳልን? የአቶ ጃዋር መሃመድ የመሪነት ደረጃ ይሄው ነው። መሪነት ማለት በዚህ እንዲህ በሆነ መልኩ ይገለጻል። ለዚህ ነው እንግዲህ በብሄራዊ ደረጃ „የቄሮ ምክር ቤት“ ለማቋቋም ጥናት ላይ መሆኑ የተደመጠው። ተረኞቹ ታራጆች ደግሞ ጠብቁ … ለዚህ አረመኔነት ነው እንግዲህ ከአዲስ አባባ እስከ ባህርዳር ድረስ ሚዲያዎችም፤ ባለስልጣኖችም ሥራ አጥተው ከፍ እና ዝቅ ሲሉ የባጁት፤ ለነገሩ ይህ መጀመሪያው ነው።  ገና የሚፈነዳ ሌላም ነገር ይኖራል። ከዚህ ሌላ ደግሞ ምን ሌላ ልትሉ ትሉኝም ይሆናል፤ ጭካኔ እኮ ሰው መሆን ማለት አይደለም። ሰው ከሰውነት ደረጃ ሲወጣ ነው ጨካኝ የሚሆነው።

ኪናዊ ጥበቡ የሰጠን ልዩ የህሊና ሽልማት!

ምስል
ያዝልቀው በሁለገብ  የእኛዊነት የመንፈስ ቤተኝነት! „ይህ ሁሉ የሆነብሽ እኔን ስለተውሽ አይደለምን? ይላል እግዚአብሄር አምላክሽ።  አሁንስ የሺሖርን ውሃ ትጠጪ ዘንድ በግብጽ መንገድ ምን ጉዳይ አለሽ? የኤፍራጥስንም ውሃ ትጠጪ ዘንድ በአሦር መንገድ ምን ጉዳይ አለሽ? ክፋትሽ ይገስጽሻል፤ ክዳትሽም ይዘልፍሻል፤ አምላክሽንም እግዚአብሄር የተወሽ እኔንም መፍራት የሌለብሽ ክፉና መራራ ነገር አንደ ሆነ እውቂ፣ ተመልከቺ፣ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሄር“ ከሥርጉተ ©ሥላሴ 12.08.2018 ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ። እፍታ እንደዛሬ። እነ ቅኖች እንዴት ቆያችሁልኝ? መቼም ሐሤት ሲኖር ፍንክንክ ስለሚያደርግ አሁንም ቅድምም እንዳያመልጥ በዛ ዙሪያ ብዙ መስራት ይጠበቅብናል። የተራራቀ መንፈስ በእሱ በአንድዬ ሃይል ራሱ በኪነ - ጥበቡ ድልድዩ እዬተሰራ ነው እና። የፈረሰው የልዩነቱ ግድግዳ ነው፤ ፈረሰ ሙሉ ለሙሉ እኔ ማለት አልችልም።  በሴራው ውሰጥ ሆነን፤ ሰው በማጥፍት ውስጥ ሆነን ማዕደኛ ስለምንሆን ነው። እጅ ለእጅ መያያዙ በአንዱ ቅን መንፈስ ውስጥ ሌላው መኖሩን ሳያረጋግጥ ነው አለሁኝ ብሎ አጁን የሚዘረጋው።  የሰሞናቱ ትዕይንት የሳዬን ይህንኑ ሃቅ ነው። የአባቶቻችን የአብርሃም፤ የይህሳቅ አምላክ ግን አሁንም አልረሳንም። የማንደራደርበት ዋናው ነገር ኢትዮጵያ ፈጣሪ ከጥፋት የሚታደጋት መሆኑን ነው። የማንደራደርበት ሌላው ገዳይ ደግሞ አማኑኤል አማልካችን ኢትዮጵያን እንደሚወዳት ነው። በቸርነቱ ያተረፈን አምላክ ይመስገነው። በጸሎት እንትጋ። አቅማችን ይሄው ነውና።  ጀመርነው ወይ ቅንነትን? ተወጠን ብል ይሻላል። የወጣልኝ ሰፊታ ነበርኩኝ ወጣት እያለሁን። ለዛውም ዲዛይኔ የተለዬ ነው። ጎንደር ተወልዳ በ

"ባልተገባ ጊዜ ሰው መግደል ውድቀት ነው" ተግተን እንጸልይ!

ምስል
„ባልተገባ ጊዜ  ሰው መግደል  ውድቀት ነው።“  (ከጠ/ሚር አብይ አህመድ የተወሰደ) „አንተ ግን ወገብህን ታጠቅ፤ ተነሥም፣  ያዘዝሁህንም ሁሉ ንግራቸው፤  በፊታቸው እንዳላስፈራህ አትፍራቸው።“ ትንቢተ ኤርምያስ ምዕራፍ ፩ ቁጥር ከ፲፯ እስከ ፲፰ ከሥርጉተ©ሥላሴ 12.08.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። እምዬ ያንቺ ቅድስና ንጹሁን መንፈስ እንዲጠብቅ አምላካችን ይርዳን፤ አሜን! እንዴት አደራችሁ ዋላችሁ አረፈዳችሁ ወገኖቼ ቅኖቹ ውዶቼ። ዛሬ እንቅልፍ አጥተው የከረሙት አይኖቼ ከናፍቆታቸው ጋር ተገናኝተዋል። ጸጥ ያለ እንቅልፍ ተኝቼ አደርኩኝ። በጥዋቱም በወጉ የተለመደውን ስላደርኩም አቅም አግኝቻለሁኝ። ከባድ ጊዜ ነበር ያሳልፍኩትኝ። በስልክ ሆነ በኢሜል አማገኛቸውን ቅኖችንም ረብሻለሁኝ ማለት እችላለሁኝ። ስለምን? ተስፋ ወደ ተስፋ ቆራጭነት ከተሸጋገረ እንደ ገና አቅም አቅግኝቶ አጎልብቶ ለማውጣት እና ራዕይን ቀጣይ ለማድረግ እጅግ ከባድ ስለሆነ።    ለዘመናት የተካሄዱ ተጋድሎዎች በሰው ጥበብ ሳይሆን በልዑል እግዚአብሄር ጥበብ የተሰጠን ጸጋ፤ የተሰጠን መክሊት፤ የሁላችንም የምንለው ጥሩ የዘመን መንገድ ተስፋው አደጋ ላይ ሲወድቅ እንደ ዜጋ እንደ አንዲት ሩህሩህ ሴትም የውስጤ ማለት ይገባ ነበር።  ትናንት በቀደመው አቅማቸው ልክ በነፃነት ሆነው ጠ/ ሚር አብይ አህመድን ማዬት መቻላችን የተፈጠረ ነገር አልነበረም ዋሾዎች፤ መርዶ ነጋሪዎች የሚሉ ወገኖቼን ተመልክቻለሁኝ። የጉዳዮችን ፍሬ ነገር ሥረ ነገር እንዲት በወጀብ እንደሚመሩም አስተውያለሁኝ። እርግጥ ነው እባካችሁ ክፉ አትመኙበት ከሚል ቅንነት ሊሆን ይችላል። እንዲዳፈንም ስለሚፈለግ ሊሆን ይችላል። በሌላ በኩል አረጋጊ ነን የሚሉትም ያ