ልጥፎች

ከኦገስት 11, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

የአብይን የቅንነት ሌጋሲ ለማሰቀጠል ብቻ እንትጋ።

ምስል
የመረጋጋት ስንቅ። ከሥርጉተ ©ሥላሴ 11.-8.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ።                  „እኔ ግን በምህረትህ ብዛት ወደ ቤትህ እገባለሁ፤               አንተን በመፍራት ወደ ቅደስናህ መቅደስ እሰግዳለሁ።“                 መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ ፬ ቁጥር ፯   ከሥርጉተ ©ሥላሴ  11.-8.2018  ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። ·       መነሻዬ https://www.youtube.com/watch?v=QN9CQEMiLVE Ethiopia: [ ሰበር ዜና !] ከዶ / ር አብይ ስለ ሶማሌ ክልልና የአቡነ መርቆርዮስ ጉብኝት የተሰጠ መግለጫ ! የሆነው ሁሉ ባይሆን መልካም ነበር። ብቻ ይሄ ቪዲዮ አንፃራዊ ነፃነት ያለው ነው። መንፈሱም ጤነኛ ነው። ቀጣዮቹ ጊዘያቶች ምን ሊሆኑ እንደሚችሉ ባላውቅም ከሰነበትንባቸው ጭጋጋማ ማዕልተ ሌሊቶች የተሻለ ተስፋ ያለው ነው። መሆን ያለበት ዓለም አቀፍ ተጽዕኖው በተከታታይ ማስቀጠል ነው። የሆነው ሁሉ ለመልካም ቢሆንም አሁንም ሴራ እና ሼር ሊያርፉ ስለማይችሉ የቅኖች መንፈስ የአብይን ሌጋሲ የማስቀጠል ተግባር ላይ መታተር ያስፈልጋል። ይሄ ቁስል እዬቀራረፉ ግጭትን የሙጥን የማለትን ሂደትን አቆሞ መድንህን የሆነውን የአብይ መንፈስ በቀደመው ሃይሉ እና ብቃቱ ይቀጠል ዘንድ የላዩን ጉዞ ተግ አድርጎ ውስጣዊ የሆነ ድጋፉን በእውነተኝነት እና ስሜት መቀጠል ነው። የሆነው ሁሉ ለበጎ ነው ብለን የሚበልጠው ቀሪ ጊዜ ስለሆነ በማንም እና በምንም ቂም እና ቁርሾ ሳናበቀል በንጹህ ህሊና የአብይን ሌጋሲ ጉልበት እንዲያገኝ አቅም እንዲኖረው ማስቻል ይገባል። እያንዳንዱ የኢትዮጵያ ዜጋ ነፍሱን ከአብይ ሌጋሲ ጋር ብቻ ባያያዘ፤ ባስማ

አልደፈርም ያለው "የሹክሽኩት ዕድምታ" በሥርጉተ ዕይታ!

ምስል
እንዳፋችሁ ያድርግላቸው ያድርግልን። „ ትእዛዙን አናገራለሁ እግዚአብሄር አለኝ፣ - አንተ ልጄ ነህ እኔ ዛሬ ወለድሁህ። “ መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ ፪ ቁጥር ፯     ከሥርጉተ © ሥላሴ 11.08.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ እምዬ የአንቺ ቅዱስ መንፈስ እንኳን እንዴት ይርሳቸው?  መነሻዬ። በመጀመርታ ግን ሰንበት እንዴት ይዟችሆዋል ውዶቼ። https://www.satenaw.com/amharic/archives/62174 ከሚነሶታ እስከ አዲስ አበባ ( ከዲያቆን ዳንኤል ክብረት ) https://www.youtube.com/watch?v=mTBe-PKlESI&t=25s awaze news የሁለቱ ጹሁፍ መነሻ የጠቅላይ ሚ/ር አብይ አህመድ ጤንነትን በሚለከት ነው። ከዚህ ቀደም ጤና አዳም "ሹክሹከታ" የሚል ዜና አቅርቦ ነበር። ጠ/ ሚር አብይ አህመድ በመርዝ በተበከለ እውሃ የግድያ ሙከራ እንደተደረገባቸው የሚገልጽ።  ይህን በማስመልከት የቡድኑ ጉባኤ መሪ ዲያቆን ዳንኤል ክብረተ ግልባጩን "ለሽክሹክታ" አድርጎ ምንም የደረሰ ነገር እንደሌላ ነው ማሰተባበያ የሰጠው የሳታናው ብራና ላይ ያገኘሁት መነባንብ ጭብጥ እንደነገረኝ፤ ስም ባይጠቅስም ግን ሁለት ማህበረ ተጓዦች ድንገተኛ ህመም እንደ ነበረባቸው እና የልዩ የህክማና ቡደኑ የሥራ ጫና እንደ ነበረበት ግን አልሸሸገም።   ይህን እንግዲህ በነሲብ ይሄ ነው ያነ ነው ማለት አይቻልም። በሌላ በኩል ግን የተፈጠረ ነገር ቢኖርም ይህን እንዲያስተባብል ጫና ማደረግ ግድ ይላል። ምክንያቱም የጉዞው ሁለመና ስለነበረ ዲያቆን ዳንኤል ክብርት እንደገናም ታዕማኝነቱም የዛን ያህል ስለሆነ ህዝብ እንዲረጋጋ ተጽዕኖ እንዲፈ

ቅጽበት እና ማህበረ ቅጽበቶች ዕዳ እና ዳጦች - የማጥ ሰርጥ።

ምስል
ብልጫ ድርግም። „የጽድቄ አምላክ በጠራሁት ጊዜ መለሰልኝ፤ በጭንቀቴም አሰፋህልኝ፤ ማረኝ ጸሎቴንም ስማ።“ መዝሙር ምዕራፍ ፬ ቁጥር ፩ ከሥርጉተ© ሥላሴ  11.08.2018 ጃዋርን እንመነውን? ሌላ እድል እንስጠውም የሚል ቧልትም አለ። ማለፊያ ነው መሸቢያ። እንዲህ እንደ ሸንብራ ቂጣ ስንገላበጥ በቅጽበት ፖለቲካ ስንተራመስ ትውልድ አሳሩን ያያል። እዳ ድጥ እና ዳጥ፤ ምጥ እና ማጥ! ኢትዮጵያ እኮ አሁን እዬጠፋችን ነው። በፈረስች አገር ነው ሽርጉዱ። ብቻ የሳምንቱ የሚዲያ ጠ/ ሚሮቻችን ደግሞ እነ አቶ ጃዋር መሃመድ ናቸው።  ማመንም አለማምንም የራስ ጉዳይ ነው። እኔ ብአዴን አብሶ የአቶ ገዱ መንፈስ ይሄን ያህል በውልቅ የፖለቲካ ቁመና ላይ መሆኑን በፍጹም አላውቅም ነበር። የእውነት በፍጹም። ጃዋርውያን ሆኖ ጠብ እርግፍ ሲል፤ ያን ያህል ተነጥፎ ደጅ ደጭ ሲል ግርም ይለኛል። እነዚያ የሚዲያ ሽፋን ያላገኙ ተክድነው የተቀመጡ ሊቃናተ - ሊቃውንታት ምን ይታዘቡት ይህን ገማና እላለሁ እኔ ከዚህ ሆኝ። ሰው የራሱ ክብር እኮ አለው። የክብርም ደንበር አለው። ክብር ቀፎ ቀልም የሌለው እስክርቢቶ ማለት አይደልመ። ልክ አለው መጠን። ለመሆኑ ይህን ያህል ከንቱ ነበርን ብአዴን? ይሄ አማራ መጥላቱን፤ ክርስትናን ማውገዙን አይደለም። ሰብዕናው በራሱ የአቶ ጃዋር መሃመድ ብልጭ ድርግም ስለሆነ ነው። እርግጥ ነው እንግዳ መቀበል የተገባ ነው። እሱ የእኔ ባይለንም ሰው ነው። በሰው አምሳል የተፈጠረ ነው። ላያችሁ ፈቀድኩኝ ለፖለቲካዬ ልቅና እና ክብር ስል ሲል የአባት አደሩ ቢደረግለት መልካም ነው።  ነገ አቶ ንጉሡ ጥላሁንን በ አቶ ደመቀ መኮነን ትክ ም/ ጠ/ ሚር አደርጎ ለሚያሾም የተገባ ነው። ብቻ ብቻ ያ ቆፍጣናው ንጉሦ