የሰማይ ቤት ሸንጎ አፈ ጉባኤያዊት።
አሽካካች። ከሥርጉተ ሥላሴ 14.06.2018 (ከገዳማዊቷ ሲዊዝዬ) „አቤቱ በመከራቸው ጊዜ ፈለግሁ፣ በገሰጽሠጽሃቸው ጊዜ ልመናቸውን ወደ አንተ አፈሰሱ። (ትንቢተ ኢሳያስ ምዕራፍ ፳፮ ቁጥር ፲፮“) ጨረሯ ብቻ ደረሰኝ። ምን ደረሰኝ ብቻ አዳረሰኝ። እሷ ግን አትታይም። ስብሰባ ትሆንን ? ወይንስ ሰማያዊ አልጋዋ ላይ ተኝታ … ወይንስ ጫጉላ ጊዜ ላይ ትሆን ወይንስ ከባዘቶማዋ ፍራሽ ተኮፍሳ ? ክብር ሲወድላት -- ደግሞም ሲያምርባትም የለችም። ብቻ የለችም። ግን አለች ትንፋሿ አገር ያዳርሳል። መንፈሷ ይሆን የሌለው ? ይሆናል። ምን ይሆናል ነው እንጂ። ግን ለምን ? … እእ … ለምን …. እ … ለምን …? ጠብቅኳት አልመጣችም። ለእኔ ለእራሱ የላከችው ለብ ያለ ጉድ ነው። ልም ነገር። ስትገርም። ለእናንተስ ይሄው የእኔ ዕጣ ፈንታ ደረሳችሁ ይሆን ? … አላውቅም። ቀና ብዬ ፈራ ተባ እያልኩ ተመለከትኳት … „ ነገ ሌላ ቀን ነው “ አሃ ! ብላ ጽፋለች። ቀና ብዬ ስመለከት ደግ „ ይህም ያልፋል “ ብላ ጽፋለች ? ጎሽ ! አልኩና ተረጋጋሁ። ግን ለምን ? አላውቅም። ለመሆኑ ያነብበኩትን እርግጠኛ ነውን ? „ ነገ ሌላ ቀን ነው „ ብላ ስለመጻፏ እንደ ገና አዎን እንደ ገና አሻቅቤና ሻቅዬ ሳዬው ተለውጦ … „ የማይቻለውንም መከራ ቢሆን በትእግስት ቻይው “ ብላ ጽፋልኛለች። ወይ ጉ