ልጥፎች

ከጁን 14, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

የሰማይ ቤት ሸንጎ አፈ ጉባኤያዊት።

ምስል
      አሽካካች።                                    ከሥርጉተ ሥላሴ 14.06.2018 (ከገዳማዊቷ ሲዊዝዬ)                 „አቤቱ በመከራቸው ጊዜ ፈለግሁ፣ በገሰጽሠጽሃቸው ጊዜ ልመናቸውን ወደ አንተ አፈሰሱ።                                             (ትንቢተ ኢሳያስ ምዕራፍ ፳፮ ቁጥር ፲፮“) ጨረሯ ብቻ ደረሰኝ። ምን ደረሰኝ ብቻ አዳረሰኝ። እሷ ግን አትታይም። ስብሰባ ትሆንን ? ወይንስ ሰማያዊ አልጋዋ ላይ ተኝታ … ወይንስ ጫጉላ ጊዜ ላይ ትሆን ወይንስ ከባዘቶማዋ ፍራሽ ተኮፍሳ ? ክብር ሲወድላት -- ደግሞም ሲያምርባትም   የለችም። ብቻ የለችም። ግን አለች ትንፋሿ አገር ያዳርሳል። መንፈሷ ይሆን የሌለው ?  ይሆናል።   ምን ይሆናል ነው እንጂ። ግን ለምን ? … እእ … ለምን …. እ … ለምን …? ጠብቅኳት አልመጣችም። ለእኔ ለእራሱ የላከችው ለብ ያለ ጉድ ነው። ልም ነገር። ስትገርም። ለእናንተስ ይሄው የእኔ ዕጣ ፈንታ ደረሳችሁ ይሆን ? … አላውቅም። ቀና ብዬ ፈራ ተባ እያልኩ ተመለከትኳት …    „ ነገ ሌላ ቀን ነው “    አሃ ! ብላ ጽፋለች። ቀና ብዬ ስመለከት ደግ „ ይህም ያልፋል “   ብላ ጽፋለች ? ጎሽ ! አልኩና ተረጋጋሁ። ግን ለምን ? አላውቅም። ለመሆኑ ያነብበኩትን እርግጠኛ ነውን ? „ ነገ ሌላ ቀን ነው „ ብላ ስለመጻፏ እንደ ገና አዎን እንደ ገና አሻቅቤና ሻቅዬ   ሳዬው ተለውጦ … „ የማይቻለውንም መከራ ቢሆን በትእግስት ቻይው “ ብላ ጽፋልኛለች። ወይ ጉ