ውስጣችን እጠበው

      ውስጣችን 
        እጠበው
         በፍቅር 
          ገበታ።

                                                      ከሥርጉተ ሥላሴ 14.05.2018 (ከገዳማዊቷ ሲወዘርላንድ።)
                                     „እናንት በሩቅ ያላችሁ የወራሁትን ስሙ፤ እናንተም በቅርብ ያላችሁ ሃይለን እወቁ።“
                                                             (ትንቢተ ኢሳያስ ምዕራፍ ፴፬ ቁጥር ፲፬)

ጤፍ እንጀራ በእርጎ እኔ መች ጠልቼ፤ ? ? ?
ሲበሉ ለማዬት - ፈቃድ ተነስቼ፤ ? ? ?
ጉሮሮ ለማርጠብ እንዲህም  - ተሟሙቼ፤ ? ? ?
በእቃ ተገምቼ - እንደ ዕቃም ታይቼ 
ቢቸግረኝ እንጂ፤ ---- መች ክብር ጠልቼ!
ቢከፋኝ ነው እንጂ፣ - ስደት ተመኝቼ
መጠለያ ከፈን አፈሩን በልቼ
ቅንቅን በቋጠሮ - ዕንባነን አውግቼ።
ሲመጣ ተስፋዬ እኔኑ ሊጠይቅ፤
ጋሬጣው አየለ ቆመ በተጠንቀቅ
አንድዬ አለኃት ላዛች ቡኒ አፈር
የሰጠኃት ሚስጢር አፍልቃ ልታኖር።
ሳቅ የተፈራበት እንዲህ ያለ ዘመን
ከወዴት ይገኛል? ከሴራ ግናግን።
የሟርት አራማጆች ሲመሽም ሲነጋም
ያነን እያኘኩ ---- ሲነጋም ሲመሽም
ዋይታ ያዝነባሉ ጉምነን በመዝገን።
እባክህ ፈጣሪ አንተ የሁሉ ጌታ?
ወሳጣችን እጠበው በፍቅር ገበታ።

ኢትዮጵያዊነት ፈተናን አሸንፎ የተፈጠረ ሚስጢር።
መሸቢያ ጊዜ። 

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም።

እህት አጊቱ ጉደታ አገር ነበረች።

አብይ ኬኛ መቅድም።