ልጥፎች

ከሴፕቴምበር 2, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

አበጀ /// ሥነ ግጥም

ምስል
አበጀ። „ጥበብ ቤቷን ሠራች ሰባቱንም ምሰሶችዋን አቆመች።“ ምሳሌ ምዕራፍ ፱ ቁጥር ፩ ከሥርጉተ ሥላሴ 02.09.2018 ከገዳማዊቷ ሲዊዝዬ። ተዬት መጣህ ብዬ ትዝታን ብጠይቅ? ወደዬት ነህ ብዬ ናፍቆትን ብጠይቅ? መልሶ ላከልኝ የዘመን ዝንቅንቅ። ቆልቁለት አውርጄ አሳፈሬዋለሁ ዳገቱን አግዤ መጪ … በል ብዬዋለሁ ማተብ ከተገኜ ሰጋር እልካለሁ። ዳጥ ለዳጥ ስማስን ቅንነት ሰብዤ ግራምጣ ተገኜ ተዚህ ከተከዜ። መተከዝ ሲሳነኝ ለጥርስ ተሟገትኩኝ ሳቅ መግዛትም ቻልኩኝ በቦንዳ ተኳልኩኝ። እቴ ሆይ! እናቴ አስቲ ልጠይቅሽ? ልጅሽ በ ክ ት ነው በዝርዝር መዛቅሽ። አንች ሆይ! የኔይቱ እምት እመቤት፤ ልባም ደማሚቱ የቱ ላይ ተሟላ ያነ አብነቱ? ሲሶ እርቦ ሲሉ ሟርተኞች፤ ሲያሟርቱ ዜግነት ክፋዩ የሂሳብ ስሌቱ፤ በዝቶ ቀረመቱ ተዛነፍ እንዳይሆን ገደለኝ ስጋቱ። ነገን አስባለሁ ሞጥሬ አጥንቼ፤ ተስፋ ስለሆነ እሱንም ሞግቼ፤ ነገን እንዲሰጠኝ ባክኖት‘ ረትቼ። ትውልደ - ድርሻዬ የእኔ መሆን በጀ፤ መታከት ለሁሉ እንዲህ እያባጀ፤ እያባጃ … የተዛነፍ ሚዛን  አይባል አበጀ፤ ትርፉ መልካምነት ሰውነን ያበጀ። ተጣፈ አሁን 20.46 ስለምን ተጣፈ /// ልብ ለልብ አሰኝቶኝ። ኢትዮጵያዊነት ከመፈጠሩ በፊት ፈተናን አሸንፎ የተፈጠረ ሚስጢር። ውዶቼ ክብረቶቼ ኑሩልኝ። ማለፊያ ጊዜ።  

እሱን ስፈትነው // ሥነ ግጥም

ምስል
እሱን ስፈትነው … „ማስተዋልስ ድምፆዋን አትሰጥምን?“ ምሳሌ ምዕራፍ ፰ ቁጥር ፪ ከሥርጉተ ሥላሴ 02.09.2018 ከገዳማዊቷ ሲወዚዬ። ስንደቅ ሰንድቆ ሳቁን ቢልክልኝ ምንአለ አላቢው እውነት ቢሆንልኝ? ግራር እና ወይራ በአንድ ያለቃቅሳሉ ዘመን እንዲያቸው ወቄት ያሰማሉ። ዳመጦ ተዳምጦ እንዝርትስ የትስ ሲገኝ? አለሎ በአላላ፤ አለባሶ ግርሞት እንዲህ ሲሆን ጠማኝ ተጠማኝ በጠማኝ ውሎማደር ሆነ ባይታዋር ተለማኝ። እሱ ለፈጠረው ለአንድዬ እፍታ እሱ ለፈጣራት ለእንደዬ እፍታ ለድንኳን ጥላ ያዥ ለሆነው ለአንድአፍታ ቀን ይገኝ ከሆነ ስገደት ማታማታ። ሱባኤ ላይ ሆኜ ተስፋን ሳማትረው ሜትር ገዝቶ ላከ እሱን ልፈትነው። ·        ተ ጣፈ አሁን 20.22 ·        ስለ ምን ተጣፈ? ስለግራሞት ብቻ …

ከሩቅ ይጠራኛል / ግጥም

ምስል
ከሩቅ ይጠራኛል። „በውኑ ጥብብ አትጮኽምን?“ ምሳሌ ምዕራፍ ፰ ቁጥር፩ ከሥርጉተ ሥላሴ 02.09.2018 ከገዳማዊቷ ሲወዚዬ። መም ረ ር ይመረኛል፤ ልዋ ጥ ህም ብለው እንብዬው ይለኛል። ጎምዝዞ ይዞኛል፤ ልፈትነው ስልም አይሆንም ይለኛል። ደማኖም ታ ጥ ቆኛል፤ ልቀቀኝም ስለው ል ሽ ሽ - ልሰልቅ ሽ እንዲህም ይለኛል። ይለኛል ይለኛል፤ መንሹን አስልፎ ክንደኛ ብሎኛል። ተረከዝ ተጎርዶ ራመድ ክዶኛል፤ መክዳቱ ክዳቱ ክዳኑ ጥፎኛል። በትርፈኛ ዘይቤ ዜማ ቀንጥ ቦ ኛል፤ ፈር ተገብ ስለሆንኩ ዓይነት ቀን ድ ቦኛል። ይሆናል አይሆንም „አይም“ ያምርብኛል „እሺ“ ቢቀርበት እንቆቆ ልኮ ኛ ል። ለእሷ ከሆነማ፤ ንጋትና ዕውነት ከሩቅ ይጠረኛል ለሚዛንም ቀኑ ናፍቆቱ ይዞኛል፤ ሸው እንዲያው ሽው እሱን ያሰኘኛል የእኩልነት ማ ዶ ት ሁሌም ይር በ ኛል። ተጣፈ አሁን 19.58። ስለምን ተጣፈ? ስለግራሞት ብቻ …

እናት የክት እና የዘወትር ልጅ የላትም ...

ምስል
ሾጣጣ። „ልጄ ሆይ ቃሌን ጠብቅ፤ ትእዛዜንም በአንተ ዘንድ ሸሽግ።“ መጽሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ ፯ ቁጥር ፩ ከሥርጉተ©ሥላሴ 02.10.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። ሾጤ - ሞጤ - ሽም ጤ  - ሾጣጤ - ሞጣጤ  - ሞጥሟጤ። ሁሎችም ቃሎች ናቸው። ሁሎችም እኩል መብት እና ግዴታ አለባቸው። ሁሎችም የአማርኛ ቋንቋ አባልተኞች ሽሙንሙኖች፤ ሸባላዎች፤ ሸንቃጣዎች ናቸው። ሁሎችም የስዋሰው ቤተኞች ናቸው። ሁሎችም መነሻቸው ከአማርኛ ፊደላት ነው። ሁሎችም ባለድምጽ፤ ባለ ቃና፤ ባለ ደንብ፤ ባለ ጌጥ፤ ባለ ዘለበታዊ ምት፤ ባላ ዜማ ናቸው። እኩል ናቸው ማለት ነው። እኩልነት እንዲህ ሲገልጥ የልብ ያደርሳል።  ኢትዮጵያዊነት እንዲህ ቢሆን ምኞቴ ነው። በመኖር እና በመኗኗር መሃከል ግን መኖር ለሁሉ ተፈጠረ፤ ግን ለሁሉ ለመሆን አቅመ ቢስ ነው። ስለሆነም መኖር ወይ እረኛ ነው ወይ ደግሞ የታገተ ነው። ወይ ደግሞ ዲዳ ነው ወይ ደግሞ ሰውር ብቻ።  „አይዋ መኖር“ ተብሎ ሲጠራ „አለሁ ለሁሉም“ ሲል ይደመጣል፤ አንዱን ሲያንጠለጥል አንዱን ሲያፈርጥ አንዱን ሲካለ ሌለውን ሲከውን፤ አንዱን ሲያቆምስ ሌላውን ሲያሰምጥ ብቻ አለሁኝ፤ አኗኗርኩኝ፤ ተኖርኛ ጋር ሆንኩኝ ይለናል ወገኛ በሉት ///  አሁም ማን ይሙት አይዋ መኖር አለሁኝ ለሁሉ፤ ሁለማንም ሆንኩኝ ሊል ነውን? አብሶ ለእጣ የለሾች ባለሾጣጣ ዕጣ ፈንታዎች አዳብለኳቸው ቢል ይመረጣል። አይዋ መኖር ግድዬለሽ ነው። አንዱን ሲያገዝፍ ወይንም ሲያስገዝፍ ሌላውን ደግሞ አጫጭቶ ሲያከስም ወይንም ሲያስተንን፤ አንዱን ባለዝናር ሲያደርግ እና አኮፍሶ ሲያስጀግን ሌላውን ትጥቅ አልቦሽ አድርጎ በዳዴ አንበርክኮ ሲያስኬደው አኗናርኩት፤ ከእኔ ወዲያ እኩልነት እና ነፃነት አዳይ ላስር ብሎ

እናላችሁ ... ስለ አቶ መላኩ ፈንታ/ ቴ

ምስል
ሚዛናዊ ሆነ የማዬት ተደሞ። „የሰው ልብ መንገድን ያዘጋጃል፤ እግዛበሄር ግን አካሄዱን ያቃናለታል።“ ምሳሌ ምዕራፍ ፲፮ ቁጥር ፱ ከሥርጉተ©ሥላሴ 02.10.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። ·        መነሻ። https://www.youtube.com/watch?v=SDNaiNMzENY „አቶ መላኩ ፈንታ የአቶ በረከት ስምኦንን ሚስጢ ዘረገፉት“ ·         መ ቅድመ ተደሞ። ዛሬ ፏ ብሏል። ፏ ብሏል ስላችሁ ግን ልዕልተይ ተገኝታለች ማለቴ አይደለም። እሷ የለችም። ፊታውራሪ የሰማይ መስኮትም በበቀኝ ዛሬ ቀና ሆኗል። ካፌያ ነገረሩንስ ሳይቀር ተቆጠብ ብሎ ደንግጓል እንደማለት። ኮነሬል ዳመናም እስቲ ይሁናችሁ ብሏል። ስለሆነም አዬሩ የሚመች ብርሃን ያለበት ብራ ሆኗል እላችሁአለሁኝ። ግን እንዴት ናችሁ የኔዎቹ ውዶቹ ነፍሶቹ? ደህና አላችሁልኝ ወይ? ኢትዮጵያዊነት እኔን መጨመረ አለበት - እናንተንም። እኔን መጨመር ያልቻለ ኢትዮጵያዊነት፤ እናንተንም መጨመር ያልቻለ እትዮጵያዊነት በአፍንጫዬ ይውጣ ትላላች ሥርጉትሻ። ስንቱን ነገር እምቅ አድርጋ ተሸክማ መኖሯን እሷና እና ጥቂት ቅን ወገኖቿ ያውቁታል እና። እራሱ አካሉን፤ ስደተኛ ወገኑን፤ ጤና ያጠውን ወገኑን ሰርዞ፤ ሲያስድድ የነበረው ሁሉ ተቆጥሮ ነው ኢትዮጵያዊነት የሚበለው። በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ የወገንን ሰብዕና ምሶ ሲቀብር የኖረው፤ አጋጣሚውን ሲያገኝ ከራሱ ክብር እና ዝና በስተቀር፤ የሌላውን ውስጣዊ፤ ማህበራዊ ሰላም ሲጨምቅ የኖረው ሁሉ ልሙጡን አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ሰንደቅ ዓላማ ስለለበስ ለሥርጉተ የታይታ እንቆቅልሽ ነው - ነገረ ተረብ።  ኢትዮጵያዊነት አስተዋይነት ነው። ኢትዮጵያዊነትም ሚዛናዊነትም ነው። መጀመሪያ ስደተኛ ወ