ልጥፎች

ከሜይ 7, 2025 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ጎንደሮች ምከሩ። ማስተዋልን ዘክሩ።

ምስል
  ጎንደሮች ምከሩ። ማስተዋልን ዘክሩ።   "አቤቱ በመመስገኛህ ቦታ በጽርሐ አርያም ሆነህ እኛን በዓይነ ምህረትህ ተመልከት።" (መጽሐፈ ባሮክ ምዕራፍ ፪ ቁጥር፭)   የእኔ ክብር ቤተሰቦች እንዴት ሰነበታችሁ? ሰንበት እንደምን አለፈ? እኔ አምላኬ ክብሩ ይስፋ ደህና ነኝ። እናንተም ደህና ሁኑልኝ። አሜን። በጣም ዘለግ ያለ ጹሁፍ ነው።      ……… እንሆ ዛሬ ………   በእቴጌ ጎንደር ዙሪያ ትንሽ እል ዘንድ ፈቀድኩኝ። በ2014 እአአ በደጉ ዘሃበሻ እና ደጉ ሳተናው የጎንደርን ተሳትፎ በሙሉ ልባቸው በተቀበሉ ድህረ ገጾች በ፬ ክፍል ስለ ጎንደር ጽፌ ነበር። የወልቃይት ጠገዴ ጉዳይንም አንድ ቀን ሊፈነዳ የሚችል የተዳፈነ ቦንብ እንደሆነ ኮልሜ ነበር። ከሁለት ዓመት ቆይታ በኋላ በኽረ ብሄራዊ ዓለም ዓቀፋዊ አጀንዳ ሆኖ ቀጥሏል።   ምን ለማለት ነው ይሄ? አስፈላጊ ሲሆን እቴጌ ጎንደርን በሚመለከት ይጣፋል ለማለት ነው። ስለ ጎንደር ሲፃፍ፤ መልካም ሲነገር የሚከፋቸው እንዳሉ አውቃለሁኝ። እነሱም ፕሮ - ህወሃቶች ናቸው። አንድ ግለሰብ፤ አንድ ተቋም፤ አንድ ሚዲያ ተግቶ በፀረ ጎንደርነት ከሠራ ያ አካል ፕሮ - ህወሃት መሆኑ አስተርጓሚ አያስፈልጋችሁም። ፕሮ - ህወሃት ሆነው ኢትዮጵያኒዝም መለያችን የሚሉትም፦ ጎንደርን ከልባቸው ፈግፍገው፦ ፍቀው ስለመሆኑ ልብ ልትሉት ይገባል። ስለምን? ጎንደር ትቀደምልኝ የሚለው ኢትዮጵያን ስለሆነ፤ የኢትዮጵያ ምልክት ነኝ የሚል ሁሉ ከጎንደር መንፈስ ጋር ግብግብ ፈጽሞ አይገባም እና።   #የቅኔው የጎጃም ህዝብን በሚመለከት።   ጎንደሬ ነኝ የሚል ሁሉ በማስተዋል ሊራመድ የሚገባው የጉዞ ቅያሴ፦ የቅኔው ጎጃምን ማገዶነት ስለጎንደር ከውስጡ በዶግማነት ሊቀበል ይ...

ፈላስፊት ኢትዮጵያ የባህር በርም፤ የወደብ ፍላጎቷንም ለመግለጽ #የማንም #ፈቃድ አያስፈልጋትም!

ምስል
  ፈላስፊት ኢትዮጵያ የባህር በርም፤ የወደብ ፍላጎቷንም ለመግለጽ #የማንም #ፈቃድ አያስፈልጋትም!    "የቤትህ ቅናት በላኝ።"     የማከብራችሁ የአገሬ ልጆች እንዴት አደራችሁ፤ እንደምንስ ዋላችሁ? በብዙ ብሄራዊ ጉዳይ በጣም ዘለግ ላለ ጊዜ ማድመጥን ብቻ ፈቅጄ #ሳደማምጥ ባጀሁኝ። አቅም ማፍሰስ ለትርፍ እና ለስኬት፤ #ለመደማመጥ እና ለትውልድ ተስፋ እርካብ ካልሆነ አቅምን ቆጠብ አድርጎ ማስተዳደር እንደሚገባ በጽኑ እያመንኩበት መጥቻለሁኝ። በተለይ የግለሰብ ሰብዕና ግንባታ ላይ ጊዜን ማባከን የተገባ አለመሆኑንም በከብት ግባት ተረድቻለሁኝ። ምስጋና ቀርቶ የተማገድንለት ሰብዕና ለሰባዕዊነት ጋሻ ለመሆን አለመትጋት ለባተሌወች ዱላ ነው። ተቀጥተንበታል። አይደገምም።    እኔም ሆንኩ ቤተሰቦቼ በአገሬ ኢትዮጵያ በጎንደር ከተማ ተወልደን ስናድግ፤ እኔ ሥራም በያዝኩበት ወቅት ኢትዮጵያ ሁለት ወደብ እንደ ነበራት አውቃለሁኝ። #አሰብ እና #ምጽዋ ። በየትኛው ዘመን እንደተሠራ ባላውቅም ጎንደር ደብረብርኃን ሥላሴ ፊት ለፊት ካለው የእመቤታችን አድህኖ ሥዕል #ጁቡቲ የኢትዮጵያ አካል እንደነበረች ያመለክታል።   በዘመነ ህወሃት በእጃችን የነበሩ ሁለት ወደቦች ለኤርትራ አገርነት ተሰጠ። የባህር ሃይሉም ጉዳይ በዝም ብሎ ተቋጬ። ወደቦችን ለማልማት የተከፈለው ዋጋ ይሁን፤ የመርከቦች ዕጣ ፋንታ አቤቱ ህወሃት ከኤርትራ መንግሥት ጋር በምን እንደቋጨው መረጃው የለኝም። የሆነ ሆኖ በዘመነ ህወሃት ለኢትዮጵያ የወደብ አማራጭነት ተነስቶ ሁሉም ለኤርትራ መሰጠቱ ብቻ ሳይሆን፦ ስለ ወደብ ማንሳት የሚያሳስር፤ የሚያስቀጣም ነበር። ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ ምን አስበው እንደ ሆነ ባላውቅም ስልጣን እንደያዙ የባህር ኃ...