ልጥፎች

ከማርች 22, 2023 ልጥፎች በማሳየት ላይ

የቤርሙዳ ትርያንግል የገመና አንግል።

ምስል
  ዕለተ ሰኞ ማዕዶተ ጠባቂ በከበቡሽ የቁራሽ እንጀራ ብራና በቢሆነኝ የተብራራ ብራ በሰብለ ህይወት አዝመራ ለራህብ የሚራራ። "ዝም ብዬ የመከራዬን ቀን እጠብቃለሁ።" (ትንቢተዕንባቆም ምዕራፍ ፫ ቁጥር ፲፯)     የቤርሙዳ ትርያንግል የገመና አንግል። የማግስት አራሙቻ የገዳይ ማህበር ስልቻ መቃብር ቆፋሪነት ብቻ። ማህበረ ደራጎን በፍርሰት በውድቀት ዝምንምን። የዘመን ቅርሻ የንቅለት ዋሻ የድንጋይ ዘመን ግርሻ። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 22/03/2021 12/11 ቪንተርቱር ሲዊዘርላንድ። የሞት ነጋሪት ታንቡር የሚነቀልበት ዕለት ናፈቀኝ።

የዋይታ አለቃ

ምስል
  ዕለተ ሰኞ ማዕዶተ ጠባቂ በከበቡሽ የቁራሽ እንጀራ ብራና በቢሆነኝ የተብራራ ብራ በሰብለ ህይወት አዝመራ ለራህብ የሚራራ። "ዝም ብዬ የመከራዬን ቀን እጠብቃለሁ።" (ትንቢተዕንባቆም ምዕራፍ ፫ ቁጥር ፲፯)     የዋይታ አለቃ ክብሩ ወላቃ። የኡኡታ ማህንዲስ ግርድስ የዕብለት ፍሩንድስ። ሥርጉተሥላሴ SerguteSelassie 22/03/2021 12/02 ቪንተርቱር ሲዊዘርላንድ። ዕብለት ስንቃቸው የሆኑ መሪ ገለሙኝ! ጎፈነኑኝ።

አገር በጨካኞች ታፍና አገር በጠላት እጅ ወድቃ

ምስል
  ዕለተ ሰኞ ማዕዶተ ጠባቂ በከበቡሽ የቁራሽ እንጀራ ብራና በቢሆነኝ የተብራራ ብራ በሰብለ ህይወት አዝመራ ለራህብ የሚራራ። "ዝም ብዬ የመከራዬን ቀን እጠብቃለሁ።" (ትንቢተዕንባቆም ምዕራፍ ፫ ቁጥር ፲፯)       አገር በጠላት እጅ ወድቃ   ቃ ብሎ በደረቀ አመራር ተደቅታ በድብልቅልቅ ተሰልቃ ደቃ! አገር በጨካኞች ታፍና ተቀምታ ታምቃ መፈናፈኛ አጥታ በዋይታ ተደፍታ ህምታ! አገር በወራሪ ተቁላልታ በዴሞግራፊ ተንቃቅታ በመደፈር ተብቃቅታ ህቅታ! አገር በፋሽት ተሰቅዛ ኤሉሄን ተናዛ ውርዴትን አርግዛ በክህደት ተገርዛ። እግዚኦ አለች አነባች ቋቷ ሞልቶ ኡኡታን ተመገበች ታፈነች፣ አምላኳን ተማፀነች ቀን ተዘርፎ ባዘነች ተንተከተከች። ሥርጉተሥላሴ SerguteSelassie 22/03/2021 11/57 ቪንተርቱር ሲዊዘርላንድ። ዕብለት ስንቃቸው የሆኑ መሪ ገለሙኝ! ጎፈነኑኝ።

ዕብለት ስንቃቸው የሆኑ መሪ ገለሙኝ! ጎፈነኑኝ።

ምስል
  ዕለተ ሰኞ ማዕዶተ ጠባቂ በከበቡሽ የቁራሽ እንጀራ ብራና በቢሆነኝ የተብራራ ብራ በሰብለ ህይወት አዝመራ ለራህብ የሚራራ። "ዝም ብዬ የመከራዬን ቀን እጠብቃለሁ።" (ትንቢተዕንባቆም ምዕራፍ ፫ ቁጥር ፲፯)     ዝንቅንቅ ድብልቅልቅ ቅይጥጥ ውጥንቅጥ። የሃሰት ቅጥቅጥ። ምንቅርቅር። ሙርቅርቅ ፍርክርክ ዝርጥርጥ የዕብለት ልቅልቅልቅ። ውልቅልቅውልቅልቅውልቅልቅ ፍጥርቅርቅ። ሥርጉተሥላሴ SerguteSelassie 22/03/2021 11/21 ቪንተርቱር ሲዊዘርላንድ። ዕብለት ስንቃቸው የሆኑ መሪ ገለሙኝ! ጎፈነኑኝ።

ገዳይ ባይቀጥፍ

  ዕለተ ሰኞ ማዕዶተ ጠባቂ በከበቡሽ የቁራሽ እንጀራ ብራና በቢሆነኝ የተብራራ ብራ በሰብለ ህይወት አዝመራ ለራህብ የሚራራ። "ዝም ብዬ የመከራዬን ቀን እጠብቃለሁ።" (ትንቢተዕንባቆም ምዕራፍ ፫ ቁጥር ፲፯) ገዳይ ባይዋሽ? ሽብሽብ። ገዳይ ባይቀጥፍ ጥልፍልፍ። ገዳይ ባያብል ዕምልምል። የዘመን ብል የፍዳ ገደላገደል የሉባ ግልገል ግምልምልግምልምልግምልምል - ልል። ሥርጉተሥላሴ SerguteSelassie 22/03/2021 11/21 ቪንተርቱር ሲዊዘርላንድ። ዕብለት ስንቃቸው የሆኑ መሪ ገለሙኝ! ጎፈነኑኝ።

መናኛ!

ዕለተ ሰኞ ማዕዶተ ጠባቂ በከበቡሽ የቁራሽ እንጀራ ብራና በቢሆነኝ የተብራራ ብራ በሰብለ ህይወት አዝመራ ለራህብ የሚራራ። "ዝም ብዬ የመከራን ቀን እጠብቃለሁ" (ትንቢተ ዕንባቆብ ፫ ቁጥር ፲፯) መናኛ! መጋኛ! የከንቱ ውዳሴ ዘበኛ። ሥርጉተሥላሴ SerguteSelassie 22/03/2021 11/14 ቪንተርቱር ሲዊዘርላንድ።  

"እኛ ባዕድ ነን"

ምስል
  ዕለተ ሰኞ ማዕዶተ ጠባቂ በከበቡሽ የቁራሽ እንጀራ ብራና በቢሆነኝ የተብራራ ብራ በሰብለ ህይወት አዝመራ ለራህብ የሚራራ "ሰባኪው ከንቱ፥ ከንቱ፥ ከንቱ፥ የከንቱ ከንቱ ሁሉም ነገር ከንቱ ይላል።" (መክብብ ፩ ቁጥር ፪)   "እኛ ባዕድ ነን" ሥንኙ በደንብ ከውስጥ ይነበብ። ኢትዮጵውያን ባዕዶች ነን። ስንት አዬነ አቃፊነት? ድንቄም? በፍርሰት፣ በንደት፣ በውድመት፣ በቀውስ፣ በቃጠሎ፣ በማተራመስ፣ በክህደት፣ በበቀለኝነት የበቀለ ትውልድ የለም። የከሰለ እንጂ። ኢትዮጵያን አከሰሏት፣ ከክብሯ አውርደው ሰቀዟት። አቅመ ቢስ ደካማ፣ ሰነፍም። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 22/03/2021 የመቃብር ሥፍራው አብይዝም ከሥሩ የሚነቀልበት ቅዱስ ዕለት ናፈቀኝ።

የሬሳ ሃሳብ ተሸካሚ

  ዕለተ ሰኞ ማዕዶተ ጠባቂ በከበቡሽ የቁራሽ እንጀራ ብራና በቢሆነኝ የተብራራ ብራ በሰብለ ህይወት አዝመራ ለራህብ የሚራራ። "ዝም ብዬ የመከራን ቀን እጠብቃለሁ።" (ትንቢተ ዕንባቆም ምዕራፍ ፫ ቁጥር ፲፯) "ከባለቤቱ ያወቀ ቡዳ ነው" የጎንደር ብሂል ነው። የኦነጉ ማህበር የገለጠውን ሃቅ የዳጠው የክህደት ባቡር የኢትዮጵያ ፍርሰት ህልመኛ ነው። እራሱም ፍርስራሽ ራዕዩም ፍርስራሽ። የሬሳ ሃሳብ ተሸካሚ መቆሚያ ጀርባ የለውም። ላንቁሶ ነው። ዘመንህን ሁሉ በኢትዮጵያ እና በኢትዮጵያዊነት ላይ ቁማርተኛ ሆነህ አሁንም ለፍርስራሹ ራፊ ይሰጠኝ ጎንድ ተክለሃይማኖት ያሰኛል። እንደ ደግነት ማፈር የተሰደደባት አገር ናት ኢትዮጵ። መጥኒ ለእሷ። ጄኒራል ከማል ገልጁ የዘለቁትን ዕውነት ማን ይድፈረው? ማህበረ ፈሪ የደራጎን ፍርፋሪ! ገና ከዚህም በላይ ሰቆቃ ሱባኤ ላይ ናቸው የአብይዝም ኦርኬሰተር ባንድ። ማህከነ! ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 22/03/2021 የትውልድ ዕዳ እንዲህ ከሜዳ!

ስድብ እና ተጋድሎ? ቦክስ እና ተጋድሎ? ጥላቻ እና ተጋድሎ?

ምስል
ዕለተ ሰኞ ማዕዶተ ጠባቂ በከበቡሽ የቁራሽ እንጀራ ብራና በቢሆነኝ ብራ በሰብለ ህይወት ብራ ለራህብ የሚራራ። "የሰው ልብ መንገድን ያዘጋጃል እግዚአብሔር ግን አካሄዱን ያቃናለታል" (ምሳሌ ፲፮ ቁጥር ፱)   ዛር ማዕዶተ ጠባቂ ነው። ህሊናዬ ያሰኜውን አጀንዳ የሚስተናገድበት። ያደሩ አጀንዳዎች፣ ሊቀድሙ የሚገባቸው አጀንዳዎች፣ ያልተቋጩ አጀንዳዎች ሁሉም ይለፍ አላቸው። ስድብ እና ተጋድሎ? ቦክስ እና ተጋድሎ? ጥላቻ እና ተጋድሎ? አድመኝነት እና ተጋድሎ? መረጋገም እና ተጋድሎ? ቂም እና ተጋድሎ? በቀልና ተጋድሎ? ተከላሎ እና ተጋድሎ? ተቧድኖ እና ተጋድሎ? የገመና ዝርዝር የተስፋ ግርር የራዕይ በረዷማ ግግር። የመቃብር ሥፍራውን አብይዝም፣ ማህበረ ጥፋቲዝምን ለመሞገት ሦስት ዓመት፣ ሦስት ጊዜ 365 × 3= ? ቀናት፣ በዛ ውስጥ ያሉ ሰዓታት፣ ደቂቃት ሁሉ ጭካኔ፣ ግፍ በደል ሲመረት ስለባጄ የግፍ ቅደም ተከተል መበራከት ይቸግረን ካልሆነ ይህን የመቃብር ሥፍራ በአመክንዮ ለመሞገት አቅም አለን። ትርፍ ነገር፣ መራከሱ አይበጅም። አክሰሱ ላላቸው ታዳጊ ወጣቶችም አረም አምራች ነው። ከሊቅ እስከ ደቂቅ አቧካሹን በህቡ አደራጅቶ ሲያፋልም ዘመን ጥሎን ሄዶ ድህነታችን አልበቃ ብሎ ሰው የሚበላ ሥርዓት ተፈጠረ። አብረን እንፈር። ከዚህ መማር ያልቻለ ሱፍ እና ከረባቱን፣ ሽብሽቦውን አውልቆ ከፖለቲካው ዓለም ሊሰናበት ይገባል። ዕድሜ ዘመን ሞገድን ተማምኖ እንኩሮ ሲያነኩር ከሚባጅ። እዬጠፋህ ጥፋትህን የሚያፋጥን ክፋ ተግባር መታመም ነው። መተላለፍም እንዲሁ። ኢትዮጵያ የሚለው ሥያሜ ሥርዓተ ህግጋት ነው። እራስን ጥሶ አገራዊነት የለም። "ልብ አምላክ ዳዊት ህግ ተላላፊዎችን ጠላሁ ይላል።" ይህ ምስባክ እኛ እንድንበት ዘንድ ነው ለክርስትና አማንያን።